የማርያም ቅዳሴ ገፅ ፲፬

ከውክፔዲያ

የማርያም ቅዳሴ ገፅ ፲፬

ዘቅዱስ ሕርያቆስ


፹፱ ፤ ቀሳውስት እጆቻችሁን አንሱ ።
፺ ፤ ያን ጊዜ ኢየሱስ ክርስቶስ ቅዱሳት ብፁዐት በሚሆኑ እድፍ በሌለባቸው እጆቹ ኅብቱን አነሣ ።
፺፩ ፤ እናምናለን ይህ እርሱ እንደሆነ በውነት እናምናለን ።
፺፪ ፤ ወደ ሰማይ ወደ አባቱ ቀና ብሎ አየ የወለደውንም ማለደ ። ደቀ መዛሙርቱንም ከክፉ ሁሉ ይጠብቃቸው ዘንድ አደራ አስጠበቀ ። ብሩክ ሲሆን ባረከ ። ቅዱስ ሲሆን ቆረሰ ።
፺፫ ፤ ከዚያም በኋላ ኅብስቱን ሳይለየው ከአምስት ላይ ያንቃው ።
፺፬ ፤ ለደቀ መዛሙርቱ ሰጣቸው ። ይህ ኅብስት "እማሬ" ለዓለም ሁሉ ቤዛ ሊሆን ስለናንተ የሚሰጥ ሥጋዬ ነው አላቸው ።
፺፭ ፤ አሜን አሜን አሜን እናምናለን እንታመናለንም ጌታችን አምላካችን ሆይ እናመሰግንሃለን ይህ እርሱ እንደሆነ በእውነት እናምናለን ።
፺፮ ፤ እንዲሁም ጽዋውን ሦስት ጊዜ ይባርክ ከተመገቡ በኋላ አመለከተ ። ይህ ጽዋ "እማሬ"ስለናንተ ጦር የሚያፈሰው ደሜ ነው ንሡ ጠጡ አለ ።
፺፯ ፤ ጽዋውን በቀኝ እጁ በአራቱ መዐዘን ይወዝውዘው ።
፺፰ ፤ አሜን አሜን አሜን እናምናለን ። እንታመናለን ።
፺፱ ፤ ይህን በምታደርጉበት ጊዜ የሞቱን መታሰቢያ ታደርጋላቹህ ። የትንሣኤውንም መታሰቢያ ትናገራላቹህ ።