የትነበርሽ ንጉሴ

ከውክፔዲያ

የትነበርሽ ንጉሴ በኢትዮጵያ የሕግ ባለሙያ እና የአካል ጉዳተኛ መብትቶች ተሟጋች ናት ፡ እ.ኤ.አ በ 2017 "የአካል ጉዳተኞችን መብቶችን እና ማካተቶችን በማስተዋወቅ እንዲሁም  በማኅበረሰቡ ውስጥ ያሉየአእምሮ ውቅርን መለወጥ የሚያበረታታ ሥራዋ"  ራይት ላይቭሊሁድ ኣዋርድን ተሸልማለች

የቀደመ ህይወት እና ትምህርት[ለማስተካከል | ኮድ አርም]

የትነበርሽ ንጉሴ የአይን ብርሃኗን ያጣችው በ 5 ዓመቷ ነበር ። ይህ አጋጣሚ በተወለድችበት በአማራ ክልል በስፋት ይተገበር ከነበረው ያለ አድሜ ጋብቻ  አንድታመልጥ እድሉን እንደፈጠረላት ትናገራለች። ፡፡የመጀመሪያ ደረጃ ትምህርቷን በሻሸመኔ ካቶሊክ የዓይነ ስውራን  ት/ቤት ተከታትላ ወደ ዳግማዊ  ምኒልክ ከፍተኛ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት (አካታች ትምህርት ቤት) ገብታ እስከ 12 ኛ ክፍል እዚያ ተማረች። በትምህርት ቤቱ ካላት አካዳሚክ ተሳትፎ በተጨማሪ የተማሪዎችን አማካሪ ጨምሮ ከ 6 በላይ የክለቦችን ክበባት መርታለች ፡፡ አዲስ አበባ ዩኒቨርስቲን በመቀላቀል የመጀመሪያ ዲግሪ በሕግ ሁለተኛ ዲግሪ በማኅበራዊ ሥራ አግኝ ታለች፡፡ ከመደበኛ ትምህርት ውጭ  በልዩ ልዩ እንቅስቃሴዎች ውስጥ በተከታታይ  ትሳተፋለች በዚህም  የመኢአድ የፀረ ኤድስ እንቅስቃሴን ከ2004 - 05 በመምራት በ 2006 የአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ (አአዩ) ሴት ተማሪዎች ማህበርን በመመስረት እንዲሁም የማህበሩ የመጀመሪያ ፕሬዝዳንት በመሆን  አገልግላለች ፡፡

እንቅስቃሴ[ለማስተካከል | ኮድ አርም]

ለሴት ልጆች ትምህርትን አጥብቃ በመስራቷ [1]እ.ኤ.አ. በ 2003 በደቡብ አፍሪካ የተቀበለችውን የአማኒታሪ ሽልማትን (አፍሪካዊ አጋርነት ለወሲባዊ እና ስነተዋልዶ ጤና እና የሴቶች መብቶች ) ጨምሮ ለፀረ-ኤድስ እንቅስቃሴ ባገለገለችበት ወቅት በርካታ ብሔራዊ እና ዓለም አቀፍ ሽልማቶችን አግኝታለች ። ፡፡ ወ / ሮ የትነበርሽ ከአካዳሚክ ህይወቷ ባሻገር በበጎፈቃደኝነት ከ 20 በላይ ድርጅቶች ውስጥ ያገለገለች ሲሆን ከነዚህም ውስጥ በኢትዮጵያ ዓይነ ስውራን የሴቶች ክንፍ ማህበር ለ 4 ዓመታት (እ.ኤ.አ. ከ 2003 እስከ 2007) መርታለች ፡፡ ከዚያም በመቀጠል የአካል ጉዳተኞች ኢኮኖሚያዊ መብትን ጨምሮ በተለያዩ የልማት መርሃ ግብሮች ውስጥ እንዲካተቱ ለማበረታታት የኢትዮጵያ የአካል ጉዳተኞችና የልማት ማዕከል (ኢ.ሲ.ዲ.ዲ.) የተባለ አገር በቀል ድርጅት ለማቋቋም ወሰነች ፡፡ከ2016 ጀምሮ ደግሞ  ቀደም ሲል በዓለምአቀፍ አምባሳደሮች  ቦርድ አባልነት ወክላው  ከነበረው የአካል ጉዳተኞች እና ልማት ብርሃን ለኣለም መንግስታዊ ያልሆነ ድርጅት  ጋር በመተባበር ላይ ትሰራለች [2]

                         የትነበርሽ ንጉሴ" የአካል ጉዳተኞችን መብትና ማካተት በማስተዋወቋ እና ሙሉ አቅማቸውን እንዲገነዘቡ የሚያስችላቸው አነቃቂ ሥራ  በመስራት በማህበረሰቡ ውስጥ የአስተሳሰብ ለውጥ በመፍጠሯ" [3] እ.ኤ.አ. በመስከረም ወር 2017 ላይ የተባበሩት መንግስታት ራይት ላይቭሊሁድ ኣዋርድ ፣ “አማራጭ የኖቤል ሽልማት” [4] ፡ ". ክብሩን ከKhadija Ismayilova, Colin Gonsalves, እና የአሜሪካ የአካባቢ ጠበቃRobert Bilott. ጋር  በመጋራት ተሸላሚ ሆናለች።[5]ራይት ላይቭሊሁድ ኣዋርድን በማሸነፏ እና በሄለን ኬለር ሽልማት  መንፈስ  የተበረታታችው የትነበርሽ ንጉሴ በህይወታቸው እና በስራ መስካቸው  ታላቅ ውጤት ያስመዘገቡ የአካል ጉዳተኛ ሴቶችን ለማክበር ከብርሃን  ለኣለም ጋር በመሆን ‹የእርሷ ችሎታዎች ሽልማትን› ኣስጀምራለች ፡፡ www.her-abilities-award.org

ህትመቶች[ለማስተካከል | ኮድ አርም]

  • የትነበርሽ ንጉሴ ፣ (2006) በኢትዮጵያ የአካል ጉዳተኞች መብቶች ላይ የሕግ ማሻሻያ አስፈላጊነት ፣ አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ፣ የሕግ ፋኩልቲ ፣ አዲስ አበባ ኢትዮጵያ ፡፡
  • የትነብርሽ ንጉሴ ፣ እና ፣ ራንሰም ቦብ (2008). የተባበሩት መንግስታት የአካል ጉዳተኞች መብቶች ኮንቬንሽን የድህነት ፣ በረሃብ ፥ ኣቅርቦት አጥረት አንዲሁም መገለል ዙሪያ ላይ የአንቅስቃሴ ጥሪ ፣ ኢ.ሲ.ዲ.ዲ. ፣ አዲስ አበባ ፣ ኢትዮጵያ
  • የትነበርሽ ንጉሴ ፣  (2009) የአካል ጉዳተኞች የሥነ-ልቦና ልኬቶች እና የሥራ ስምሪት ፣ አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ፣ የማኅበራዊ ሥራ ትምህርት ቤት ፣ አዲስ አበባ ፣ ኢትዮጵያ ፡፡

ሽልማቶች[ለማስተካከል | ኮድ አርም]

  • የጾታ እና የስነ ተዋልዶ ጤና ተሟጋቾች የ AMANITARE ሽልማት ፣ እ.ኤ.አ. 2003 ፣ ጆሃንስበርግ ፣ ደቡብ አፍሪካ ፡
  • የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከአዲስ አበባ ኤች.አይ.ቪ / ኤድስ መከላከያና ቁጥጥር ጽህፈት ቤት (ኤች.ፒ.ኮ.) ጋር በመተባበር እጅግ በጣም ጥሩ የኤች.አይ.ቪ / ኤድስ መከላከልና መቆጣጠር እንቅስቃሴ ማስተባበር የግለሰብ ሽልማት ፡፡ ጥቅምት 7 ቀን 2005 አዲስ አበባ ፣ ኢትዮጵያ ፡፡
  • በጄኔራል ሜዲካል ሐኪሞች ማህበር የተሰጠው ምርጥ የኤች.አይ.ቪ / ኤድስ ብሔራዊ አክቲቪስት ፣ 2005 ፣ አዲስ አበባ ፣ ኢትዮጵያ ፡፡
  • የዓለም የልዩነት 100 ሽልማት ፣ በዓለም አቀፍ የሴቶች (ቲአአዋ) ተሸልሟል ፡ [6]
  • ራይት ላይቭሊሁድ ኣዋርድ [7]
  • የሄለን ኬለር መንፈስ 2018 [1] Archived ጁን 22, 2019 at the Wayback Machine

ማጣቀሻዎች[ለማስተካከል | ኮድ አርም]

  1. ^ "Yetnebersh Nigussie". Archived from the original on 2019-04-28. በ2020-10-31 የተወሰደ.
  2. ^ "LIGHT FOR THE WORLD website, March 2016". Archived from the original on 2016-04-01. በ2020-10-31 የተወሰደ.
  3. ^ "Yetnebersh Nigussie | The Right Livelihood Award" (በen-US). Archived from the original on 2019-04-28. በ2020-10-31 የተወሰደ.
  4. ^ "'Alternative Nobel Prize' awarded to four activists, including U.S. lawyer" CBS News (26 September 2017).
  5. ^ Ismail Akwei, "Blind female Ethiopian lawyer wins global award for promoting disability rights" Africa News (27 September 2017).
  6. ^ Ethiopia Investor website
  7. ^ "Right Livelihood Award 2017 announcement". Archived from the original on 2017-11-01. በ2020-10-31 የተወሰደ.