የአራቱ ቄሣሮች ዓመት

ከውክፔዲያ

የአራቱ ቄሣሮች ዓመትሮሜ መንግሥት ታሪክ አራት ቄሣሮች በየተራቸው የተነሱበት ዓመት ወይም 69 እ.ኤ.አ. ነበር። እነኚህም አራት ቄሣሮች ጋልባኦጦዊቴሊዩስቤስጳስያን ናቸው። በኢትዮጵያ አቆጣጠር የነባሩ ቄሣር ኔሮን ራሱን ከገድለበት ወቅት ከሰኔ ወር 60 ዓም ጀምሮ ቤስጳስያን እስካሸነፈበት ወቅት እስከ ታኅሳስ 62 ዓም ድረስ የነበረው ብሔራዊ ጦርነት ማለት ነው።

የ፬ቱ ቄሣሮች ዓመት
  • 1. ጋልባ - ፯ ወር ቆየ - በሰኔ 60 ዓም በኔሮን ያመጹ ክፍላገራት፦ ጋሊያ፣ ሂስፓኒያ
  • 2. ኦጦ - ፫ ወር ቆየ - በጥር 61 ዓም የሉሲታኒያ አገረ ገዥ ሲሆን ከሮሜ ሥራዊት ጋር በጋልባ አመጸ
  • 3. ዊቴሊዩስ - ፰ ወር ቆየ - በጥር-ሚያዝያ 61 ዓም በኦጦ ያመጹ ክፍላገራት፦ ጌርማኒያ፣ ጋሊያ፣ ራይቲያ፣ ብሪታኒያ
  • 4. ቤስጳስያን - ከሐምሌ 61-ታህሳስ 62 ዓም በዊቴልዩስ ያመጹ ክፍላገራት፦ ሶርያ፣ ይሁዳ፣ ግብጽ፣ ሞይስያ፣ ድልማጥያ፣ ፓኖኒያ