የኢትዮጵያ የ5 ሺ ዓመት ታሪክ ከኖኅ እስከ ኢህአዴግ
የኢትዮጵያ የ 5ሺ ዓመት ታሪክ ከ ኖሕ እስከ ኢሀዴግ በ2003 ዓ.ም በጋዜጠኛና ደራሲፍስሐ ያዜ ካሳ የተፃፈ መጽሐፍ ነው።የኢትዮጵያን የተዘነጋ ታሪክ ሳይቀር በከፍተኛ ምርምር ያሙዋላና በብዙሃኑ አንባቢያን ዘንድ ግዙፍ አድናቆት የተቸረውም ነው።የአለም ታሪክ መነሻ ኢትዮጵያ መሆኑዋን ያረጋገጠ ከመሆኑም በላይ፤ኢትዮጵያዊ ምሁራንን ሳይቀር ያስደነቀና ያስማማ ሆኖዋል።በተለምዶ የ3ሺ ዓመት ታሪክ እየተባለ የቆየው የኢትዮጵያ ታሪክም በዚህ መጽሐፍ ተሽሮ የ 5ሺ8መቶ ዓመት ታሪክ ያላት አገር መሆኑዋ ተረጋግጦበታል። ይህ መጻህፍ የተጻፈው በጋዜጠኛና ደራሲ ፍስሐ ያዜ ካሳ ነው::
ጋዜጠኛና ደራሲ ፍስሐ ያዜ ካሳ በቀድሞው ራክማኖቭ የቴአትርና ስነጥበባት ኮሌጅ የጋዜጠኝነት ትምህርቱን ለ3 ዓመታት የተከታተለ ሲሆን ከዚያ በኋላ ደግሞ በአዲስ አበባ ዩንቨርስቲ በኢትዮጵያ ቋንቋዎችና ጽነ-ጽሁፍ Literature የመጀመሪያ ድግሪ (ባችለር ኦፍ አርት) ያለው ሲሆን ከ 2000 ዓ.ም ጀምሮ ባሉት ጊዜያት በተለያዩ የአማርኛ ጋዜጦችና መጽሔቶች በሰንደቅ ጋዜጣ፣ በአውራምባ ታይምስ፣ በመሰናዘሪያ፣ በአዲስ፣ ፕሬስ፣ በጎግል፣ እንዲሁም በቀድሞው ኢቲቪ2 እና በእዲስ አበባ F.m 96.3 ሬዲዮ እና በአዲስ ልሳን ጋዜጣ እንዲሁም በተለያዩ የፕሬስ ዘርፎች ለአስር ዓመታት በጋዜጠኝነት የሰራ ሲሆን በተወዳጅ እና አንቂ ጽሁፎቹና በጥልቅ ትንታኔዎቹ የሚታወቅ በርካታ አስተማሪ ሃሳቦችን እንዲሁም የኢትዮጵያን ታሪክ የሚመለከቱ አርቲክሎችን ወደ አንባቢያን ሲያደርስ የነበረ ነው::
ቀጥሎም በ2003 ዓ.ም የኢትዮጵያ የ 5ሺ ዓመት ታሪክ ከኖኅ እስከ ኢህአዴግ" ቁጥር 1" እና በ2004 ዓ.ም የዚሁ ተከታይ ክፍል የሆነው ቁጥር 2 "ካልተዘመረለት ኢያሱ እስከተዘመረለት ኢህአዴግ" የሚሉ የኢትዮጵያን የ 8 ሺ ዓመታት ታሪክን የያዙ አስደናቂ መጻህፍት ያበረከተ ነው::
ቀጥሎ በ2005 ዓ.ም "እኔና ቹ" ቻይናዊቷ ፍቅረኛየ" የሚል ተወዳጅ መጽሐፍ አበርክቶዋል:: ቀጥሎ በ2007 ዓ.ም የሳጥናኤል ጎል ኢትዮጵያ ቁጥር 1. በ2009 ዓ.ም ቁጥር 2, በ2010 ዓ.ም ቁጥር 3, በ2012 ቁጥር 4 የሚሉ እጅግ ተወዳጅና መነጋገሪያ የሆኑ መጻህፍትን አበርክቶዋል::
እነዚህ መጻህፍትም በኢትዮጵያ የመጽሐፍ ሽያጭ ታሪክ ሪከርድ የያዙና እያንዳንዳቸው 200 ሺ ኮፒዎች የታተሙለት ሲሆን በአጠቃላይ ከ 2003 ዓ.ም እስከ 2013 ዓ.ም ድረስ ባሉት ጊዜያት ከ 10 በላይ ተወዳጅ መጻህፍትን ለኢትዮጵያ አንባቢያን ያበረክተ ተወዳጅ የስነ-ጽሁፍ ሰው ነው::
http://books.good-amharic-books.com/fiveshe-1.PDF
ጅምር! ይህ አጭር ጽሑፍ መሠረት ወይም መዋቅር ነው። አሁን ሊያስፋፉት ይችላሉ! |