የፌደራል የሥነምግባር እና የፀረ-ሙስና ኮሚሽን
የፌደራል የሥነምግባር እና የፀረ-ሙስና ኮሚሽን (ፌ.ሥ.ፀ.ሙ.ኮ.) በኢትዮጵያ ሲቪል ሰርቪስ ውስጥ የሥነምግባር መከታተያ ኮሚሽን ነው። የኮሚሽኑ ተጠሪነት በቀጥታ ለኢትዮጵያ ጠቅላይ ሚኒስትር ነው።[1] የኮሚሽኑ ኮሚሽነር ክቡር አቶ ዓሊ ሱለይማን ሲሆኑ ም/ኮሚሽነሩ ደግሞ ክቡር አቶ ወዶ አጦ ናቸው። ኮሚሽኑ «ሥነምግባር» (እንግሊዝኛ፦ Ethics) የተባለ በዓመት አራት ጊዜ የሚታተም መፅሄት እና «መስታወት» (እንግሊዝኛ፦ Insight) የተባለ በዓመት ሁለት ጊዜ የሚወጣ ኒውስሌተር አለው።
አመሠራረት[ለማስተካከል | ኮድ አርም]
እ.ኤ.አ. በ1996 በብሔራዊ ደረጃ የተጀመረው የሲቪል ሰርቪስ ማሻሻያ ፕሮግራም የሥነምግባር ንዑስ ፕሮግራምን በውስጡ የያዘ ነበር።[2] የስነምግባር ንዑስ ፕሮግራም አንድ ፕሮጀክት ኮሚሽኑን ማቋቋም ነበር።[2] የፕሮጀክቱም ስም የስነምግባር መከታተያና ማዕከላዊ አካል ማቋቋሚያ ፕሮጀክት የሚል ነበር። በዚህም መሰረት የፌደራል የሥነምግባርና የፀረ-ሙስና ኮሚሽን ግንቦት 16 ቀን 1993 ዓ.ም. በአዋጅ ተቋቋመ።[2]
መዋቅር[ለማስተካከል | ኮድ አርም]
ኮሚሽኑ ዘጠኝ ዳይሬክቶሬቶችና ሁለት አገልግሎቶች አሉት። በተጨማሪም የኮሚሽኑን ውስጣዊ አሠራርን የሚከታተል የሥነምግባር መከታተያ ጽ/ቤት አለ።[3] ይህም ጽህፈት ቤት በአቶ ሃረጎት አብርሃ ይመራል።[3] የፌደራል የሥነምግባር እና የፀረ-ሙስና ኮሚሽን እስከ መጋቢት ፴ ቀን ፳፻፬ ዓ.ም. ድረስ 315 ሠራተኞች ያሉት ሲሆን ከዚህ ውስጥ 101 ሴቶች ናቸው።[4]
የፌደራል የሥነምግባር እና የፀረ-ሙስና ኮሚሽን ዋና መስሪያ ቤት አዲስ አበባ ይገኛል።[5] በድሬዳዋ ከተማ የሚገኘው የኮሚሽኑ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት የተመረቀው በመጋቢት ፲፩ ቀን ፳፻፪ ዓ.ም. ሲሆን በአሁኑ ወቅት 21 ሠራተኞች አሉት።[5]
ዳይሬክቶሬቶች[ለማስተካከል | ኮድ አርም]
ዳይሬክቶሬት | ዳይሬክተር |
---|---|
የሀብት ማሳወቂያ እና ምዝገባ ዳይሬክቶሬት[6] | አቶ ግርማ ወርቁ[6] |
የሙስና ወንጀል ምርመራ እና ዐቃቤ ሕግ ዳይሬክቶሬት[7] | አቶ ገብሩ ገበየሁ[7] |
የሙስና መከላከል ዳይሬክቶሬት[8] | አቶ አክልሉ ሙሉጌታ[8] |
የሥነ ምግባር ትምህርት እና ኮሚዩኒኬሽን ጉዳዮች ዳይሬክቶሬት[9] | አቶ ብርሃኑ አሰፋ[9] |
የሥነ ምግባር አውታሮች ማስተባበሪያ ዳይሬክቶሬት[10] | አቶ ብርሃኑ ክፈተው[10] |
የሰው ሀብት ሥራ አመራር[11] | አቶ መኮንን ዘገዬ[11] |
ዕቅድ፣ ግዥ እና ፋይናንስ ዳይሬክቶሬት[12] | አቶ ሙላት ሸዋታጠቅ[12] |
የጥናት እና የለውጥ ሥራ አመራር ዳይሬክቶሬት[13] | አቶ ተስፋዬ ሻሜቦ (ተጠባባቂ)[13] |
የኦዲት አገልግሎት ዳይሬክቶሬት[14] | አቶ ፋኖሴ ሀሰን[14] |
አገልግሎቶች[ለማስተካከል | ኮድ አርም]
አገልግሎት | ኃላፊ |
---|---|
የህግ አገልግሎት[15] | አቶ ብሌን ግርማይ (ተጠባባቂ)[15] |
ጠቅላላ አገልግሎት[16] | ጥላዬ የትዋለ[16] |
በጀት[ለማስተካከል | ኮድ አርም]
ኮሚሽኑ ከመንግስት በ፳፻፪ ዓ.ም. 16.23 ሚሊዮን ብር፣ በ፳፻፫ ዓ.ም. 26 ሚሊዮን 93 ሺህ 930 ብር፣ በ፳፻፬ ዓ.ም. ደግሞ 34 ሚሊዮን 840 ሺህ ብር የተመደበለት ሲሆን ከሌሎች አለም አቀፍ ተቋማት በየዓመቱ የሚያገኘው ገንዘብም አለ።[4]
ማመዛገቢያ[ለማስተካከል | ኮድ አርም]
- ^ የፌደራል የሥነምግባር እና የፀረ-ሙስና ኮሚሽን ተጠሪነት Archived ኦክቶበር 16, 2013 at the Wayback Machine (በነሐሴ ፳፬ ቀን ፳፻፭ ዓ.ም. የተወሰደ)
- ^ ሀ ለ ሐ የፌደራል የሥነምግባር እና የፀረ-ሙስና ኮሚሽን አመሠራረት Archived ኦክቶበር 16, 2013 at the Wayback Machine (በነሐሴ ፳፬ ቀን ፳፻፭ ዓ.ም. የተወሰደ)
- ^ ሀ ለ የሥነምግባር መከታተያ ክፍል Archived ኦክቶበር 16, 2013 at the Wayback Machine (በነሐሴ ፳፬ ቀን ፳፻፭ ዓ.ም. የተወሰደ)
- ^ ሀ ለ የኮሚሽኑ በጀትና የሰው ኃይል Archived ኦክቶበር 16, 2013 at the Wayback Machine (በነሐሴ ፳፬ ቀን ፳፻፭ ዓ.ም. የተወሰደ)
- ^ ሀ ለ ቅርንጫፍ ፅህፈት ቤት Archived ኦክቶበር 16, 2013 at the Wayback Machine (በነሐሴ ፳፬ ቀን ፳፻፭ ዓ.ም. የተወሰደ)
- ^ ሀ ለ የሀብት ማሳወቂያ እና ምዝገባ ዳይሬክቶሬት Archived ኦክቶበር 16, 2013 at the Wayback Machine (በነሐሴ ፳፬ ቀን ፳፻፭ ዓ.ም. የተወሰደ)
- ^ ሀ ለ የሙስና ወንጀል ምርመራ እና ዐቃቤ ሕግ ዳይሬክቶሬት Archived ኦክቶበር 16, 2013 at the Wayback Machine (በነሐሴ ፳፬ ቀን ፳፻፭ ዓ.ም. የተወሰደ)
- ^ ሀ ለ የሙስና መከላከል ዳይሬክቶሬት Archived ኦክቶበር 16, 2013 at the Wayback Machine (በነሐሴ ፳፬ ቀን ፳፻፭ ዓ.ም. የተወሰደ)
- ^ ሀ ለ የሥነ ምግባር ትምህርት እና ኮሚዩኒኬሽን ጉዳዮች ዳይሬክቶሬት Archived ኦክቶበር 16, 2013 at the Wayback Machine (በነሐሴ ፳፬ ቀን ፳፻፭ ዓ.ም. የተወሰደ)
- ^ ሀ ለ የሥነ ምግባር አውታሮች ማስተባበሪያ ዳይሬክቶሬት Archived ኦክቶበር 16, 2013 at the Wayback Machine (በነሐሴ ፳፬ ቀን ፳፻፭ ዓ.ም. የተወሰደ)
- ^ ሀ ለ የሰው ሀብት ሥራ አመራር Archived ኦክቶበር 16, 2013 at the Wayback Machine (በነሐሴ ፳፬ ቀን ፳፻፭ ዓ.ም. የተወሰደ)
- ^ ሀ ለ ዕቅድ፣ ግዥ እና ፋይናንስ ዳይሬክቶሬት Archived ኦክቶበር 16, 2013 at the Wayback Machine (በነሐሴ ፳፬ ቀን ፳፻፭ ዓ.ም. የተወሰደ)
- ^ ሀ ለ የጥናት እና የለውጥ ሥራ አመራር ዳይሬክቶሬት Archived ኦክቶበር 16, 2013 at the Wayback Machine (በነሐሴ ፳፬ ቀን ፳፻፭ ዓ.ም. የተወሰደ)
- ^ ሀ ለ የኦዲት አገልግሎት ዳይሬክቶሬት Archived ኦክቶበር 16, 2013 at the Wayback Machine (በነሐሴ ፳፬ ቀን ፳፻፭ ዓ.ም. የተወሰደ)
- ^ ሀ ለ የህግ አገልግሎት Archived ኦክቶበር 16, 2013 at the Wayback Machine (በነሐሴ ፳፬ ቀን ፳፻፭ ዓ.ም. የተወሰደ)
- ^ ሀ ለ ጠቅላላ አገልግሎት Archived ኦክቶበር 16, 2013 at the Wayback Machine (በነሐሴ ፳፬ ቀን ፳፻፭ ዓ.ም. የተወሰደ)
የውጭ መያያዣ[ለማስተካከል | ኮድ አርም]
- ይፋ ድረ-ገጽ Archived ኦክቶበር 16, 2013 at the Wayback Machine