የፌደራል የሥነምግባር እና የፀረ-ሙስና ኮሚሽን

ከውክፔዲያ
የኮሚሽኑ ምልክት

የፌደራል የሥነምግባር እና የፀረ-ሙስና ኮሚሽን (ፌ.ሥ.ፀ.ሙ.ኮ.) በኢትዮጵያ ሲቪል ሰርቪስ ውስጥ የሥነምግባር መከታተያ ኮሚሽን ነው። የኮሚሽኑ ተጠሪነት በቀጥታ ለኢትዮጵያ ጠቅላይ ሚኒስትር ነው።[1] የኮሚሽኑ ኮሚሽነር ክቡር አቶ ዓሊ ሱለይማን ሲሆኑ ም/ኮሚሽነሩ ደግሞ ክቡር አቶ ወዶ አጦ ናቸው። ኮሚሽኑ «ሥነምግባር» (እንግሊዝኛ፦ Ethics) የተባለ በዓመት አራት ጊዜ የሚታተም መፅሄት እና «መስታወት» (እንግሊዝኛ፦ Insight) የተባለ በዓመት ሁለት ጊዜ የሚወጣ ኒውስሌተር አለው።

አመሠራረት[ለማስተካከል | ኮድ አርም]

እ.ኤ.አ. በ1996 በብሔራዊ ደረጃ የተጀመረው የሲቪል ሰርቪስ ማሻሻያ ፕሮግራም የሥነምግባር ንዑስ ፕሮግራምን በውስጡ የያዘ ነበር።[2] የስነምግባር ንዑስ ፕሮግራም አንድ ፕሮጀክት ኮሚሽኑን ማቋቋም ነበር።[2] የፕሮጀክቱም ስም የስነምግባር መከታተያና ማዕከላዊ አካል ማቋቋሚያ ፕሮጀክት የሚል ነበር። በዚህም መሰረት የፌደራል የሥነምግባርና የፀረ-ሙስና ኮሚሽን ግንቦት 16 ቀን 1993 ዓ.ም. በአዋጅ ተቋቋመ።[2]

መዋቅር[ለማስተካከል | ኮድ አርም]

ኮሚሽኑ ዘጠኝ ዳይሬክቶሬቶችና ሁለት አገልግሎቶች አሉት። በተጨማሪም የኮሚሽኑን ውስጣዊ አሠራርን የሚከታተል የሥነምግባር መከታተያ ጽ/ቤት አለ።[3] ይህም ጽህፈት ቤት በአቶ ሃረጎት አብርሃ ይመራል።[3] የፌደራል የሥነምግባር እና የፀረ-ሙስና ኮሚሽን እስከ መጋቢት ፴ ቀን ፳፻፬ ዓ.ም. ድረስ 315 ሠራተኞች ያሉት ሲሆን ከዚህ ውስጥ 101 ሴቶች ናቸው።[4]

የፌደራል የሥነምግባር እና የፀረ-ሙስና ኮሚሽን ዋና መስሪያ ቤት አዲስ አበባ ይገኛል።[5] በድሬዳዋ ከተማ የሚገኘው የኮሚሽኑ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት የተመረቀው በመጋቢት ፲፩ ቀን ፳፻፪ ዓ.ም. ሲሆን በአሁኑ ወቅት 21 ሠራተኞች አሉት።[5]

ዳይሬክቶሬቶች[ለማስተካከል | ኮድ አርም]

ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር
የሀብት ማሳወቂያ እና ምዝገባ ዳይሬክቶሬት[6] አቶ ግርማ ወርቁ[6]
የሙስና ወንጀል ምርመራ እና ዐቃቤ ሕግ ዳይሬክቶሬት[7] አቶ ገብሩ ገበየሁ[7]
የሙስና መከላከል ዳይሬክቶሬት[8] አቶ አክልሉ ሙሉጌታ[8]
የሥነ ምግባር ትምህርት እና ኮሚዩኒኬሽን ጉዳዮች ዳይሬክቶሬት[9] አቶ ብርሃኑ አሰፋ[9]
የሥነ ምግባር አውታሮች ማስተባበሪያ ዳይሬክቶሬት[10] አቶ ብርሃኑ ክፈተው[10]
የሰው ሀብት ሥራ አመራር[11] አቶ መኮንን ዘገዬ[11]
ዕቅድ፣ ግዥ እና ፋይናንስ ዳይሬክቶሬት[12] አቶ ሙላት ሸዋታጠቅ[12]
የጥናት እና የለውጥ ሥራ አመራር ዳይሬክቶሬት[13] አቶ ተስፋዬ ሻሜቦ (ተጠባባቂ)[13]
የኦዲት አገልግሎት ዳይሬክቶሬት[14] አቶ ፋኖሴ ሀሰን[14]

አገልግሎቶች[ለማስተካከል | ኮድ አርም]

አገልግሎት ኃላፊ
የህግ አገልግሎት[15] አቶ ብሌን ግርማይ (ተጠባባቂ)[15]
ጠቅላላ አገልግሎት[16] ጥላዬ የትዋለ[16]

በጀት[ለማስተካከል | ኮድ አርም]

ኮሚሽኑ ከመንግስት በ፳፻፪ ዓ.ም. 16.23 ሚሊዮን ብር፣ በ፳፻፫ ዓ.ም. 26 ሚሊዮን 93 ሺህ 930 ብር፣ በ፳፻፬ ዓ.ም. ደግሞ 34 ሚሊዮን 840 ሺህ ብር የተመደበለት ሲሆን ከሌሎች አለም አቀፍ ተቋማት በየዓመቱ የሚያገኘው ገንዘብም አለ።[4]

ማመዛገቢያ[ለማስተካከል | ኮድ አርም]

  1. ^ የፌደራል የሥነምግባር እና የፀረ-ሙስና ኮሚሽን ተጠሪነት Archived ኦክቶበር 16, 2013 at the Wayback Machine (በነሐሴ ፳፬ ቀን ፳፻፭ ዓ.ም. የተወሰደ)
  2. ^ የፌደራል የሥነምግባር እና የፀረ-ሙስና ኮሚሽን አመሠራረት Archived ኦክቶበር 16, 2013 at the Wayback Machine (በነሐሴ ፳፬ ቀን ፳፻፭ ዓ.ም. የተወሰደ)
  3. ^ የሥነምግባር መከታተያ ክፍል Archived ኦክቶበር 16, 2013 at the Wayback Machine (በነሐሴ ፳፬ ቀን ፳፻፭ ዓ.ም. የተወሰደ)
  4. ^ የኮሚሽኑ በጀትና የሰው ኃይል Archived ኦክቶበር 16, 2013 at the Wayback Machine (በነሐሴ ፳፬ ቀን ፳፻፭ ዓ.ም. የተወሰደ)
  5. ^ ቅርንጫፍ ፅህፈት ቤት Archived ኦክቶበር 16, 2013 at the Wayback Machine (በነሐሴ ፳፬ ቀን ፳፻፭ ዓ.ም. የተወሰደ)
  6. ^ የሀብት ማሳወቂያ እና ምዝገባ ዳይሬክቶሬት Archived ኦክቶበር 16, 2013 at the Wayback Machine (በነሐሴ ፳፬ ቀን ፳፻፭ ዓ.ም. የተወሰደ)
  7. ^ የሙስና ወንጀል ምርመራ እና ዐቃቤ ሕግ ዳይሬክቶሬት Archived ኦክቶበር 16, 2013 at the Wayback Machine (በነሐሴ ፳፬ ቀን ፳፻፭ ዓ.ም. የተወሰደ)
  8. ^ የሙስና መከላከል ዳይሬክቶሬት Archived ኦክቶበር 16, 2013 at the Wayback Machine (በነሐሴ ፳፬ ቀን ፳፻፭ ዓ.ም. የተወሰደ)
  9. ^ የሥነ ምግባር ትምህርት እና ኮሚዩኒኬሽን ጉዳዮች ዳይሬክቶሬት Archived ኦክቶበር 16, 2013 at the Wayback Machine (በነሐሴ ፳፬ ቀን ፳፻፭ ዓ.ም. የተወሰደ)
  10. ^ የሥነ ምግባር አውታሮች ማስተባበሪያ ዳይሬክቶሬት Archived ኦክቶበር 16, 2013 at the Wayback Machine (በነሐሴ ፳፬ ቀን ፳፻፭ ዓ.ም. የተወሰደ)
  11. ^ የሰው ሀብት ሥራ አመራር Archived ኦክቶበር 16, 2013 at the Wayback Machine (በነሐሴ ፳፬ ቀን ፳፻፭ ዓ.ም. የተወሰደ)
  12. ^ ዕቅድ፣ ግዥ እና ፋይናንስ ዳይሬክቶሬት Archived ኦክቶበር 16, 2013 at the Wayback Machine (በነሐሴ ፳፬ ቀን ፳፻፭ ዓ.ም. የተወሰደ)
  13. ^ የጥናት እና የለውጥ ሥራ አመራር ዳይሬክቶሬት Archived ኦክቶበር 16, 2013 at the Wayback Machine (በነሐሴ ፳፬ ቀን ፳፻፭ ዓ.ም. የተወሰደ)
  14. ^ የኦዲት አገልግሎት ዳይሬክቶሬት Archived ኦክቶበር 16, 2013 at the Wayback Machine (በነሐሴ ፳፬ ቀን ፳፻፭ ዓ.ም. የተወሰደ)
  15. ^ የህግ አገልግሎት Archived ኦክቶበር 16, 2013 at the Wayback Machine (በነሐሴ ፳፬ ቀን ፳፻፭ ዓ.ም. የተወሰደ)
  16. ^ ጠቅላላ አገልግሎት Archived ኦክቶበር 16, 2013 at the Wayback Machine (በነሐሴ ፳፬ ቀን ፳፻፭ ዓ.ም. የተወሰደ)

የውጭ መያያዣ[ለማስተካከል | ኮድ አርም]