ገብተሽ አልቀሽ

ከውክፔዲያ

ገብተሽ አልቀሽ

(15)አንድ ቀን ከወዳጃቸው ዘንድ ድግስ ተጠርተው ሄደው እዚያ ውለው ወደ ቤታቸው ሲመጡ አሽከራቸው በር ሲከፍት አስቀደመው አለቃ ገብተው የባለቤታቸውን መግባት ሲጠባበቁ ትንሽ ዘግየት ስላሉ «እባክሽ ገብተሽ ገብተሽ አልቀሽ እንደሆን በሬን ልዝጋበት» አሉ። የቁመታቸውን መርዘም መናገራቸው ነው።