ጎቤ መልኬ

ከውክፔዲያ

የሰው ልጅ በዚች ምድር ላይ ሲኖር ከሐብት፣ ከንብረትና ከምቾች ይልቅ ያለነጻነት መኖር እንደማይችል ታጋይ አርበኛ ጎቤ መልኬ ህያው ምስክር ነው።

ታጋይ አርበኛ ጎቤ መልኬ በታች አርማጭሆ ወረዳ በአካባቢ ህዝብ ዘንድ የተከበረ አራሽ-ነጋዴ፣ ነበር። ታጋይ አርበኛ ጎቤ አራት የጭነት አይሱዚ መኪኖች፣ ከአራት መቶ በላይ የቁም ከብቶች፣ በርካታ ቋሚና ተንቀሳቃሽ ንብረትና ሰፊ የሰሊጥ እርሻ መሬት ባለቤት፣ ከነጻነት በቀር ምንም ያላጣ ታዋቂና የተከበረ ሀገርና ወገን ወዳድ ባለሃብትና ጀግና ነበር። የህዝብ እንግለት ይብቃ በማለት ነፍጥ አንግቦ በመጨረሻ መስዋዕት እስከሆነበት የካቲት 2009 ዓ.ም ድረስ ታግሏል።