Donna Reed Show

ከውክፔዲያ
የስቶን ቤተሠብ

The Donna Reed Show (ዘ ዶና ሪድ ሾው) ከ1958 እስከ 1966 እ.ኤ.አ. ድረስ የተሠራ አሜሪካዊ የቤተሠብ ኮሜዲ ነው።

የተዋናይቱ ዶና ሪድ ሚና በፊልሙ ላይ ዶና ስቶን፣ ብልሃተኛ የሆነች እናት፣ ሚስትና አንዳንዴ ነርስ ናት። ባለቤቷም ሀኪሙ ዶ/ር አሌክስ ስቶን ደሞ ጎበዝ አባት ነው። ወጣት ልጆቻቸውም ሜሪ እና ጄፍ ይባላሉ። በዘመናቸው ለነበረው አሜሪካዊ ትዳር መልካም አራያ ስለ ሆኑ ተወዳጅነት ያገኘ ፕሮግራም ሆኖ ይታወሳል።

ይህ ፕሮግራም ዓለም አቀፍ ኢትዮጵያም ውስጥ ተሰራጭቶ ነበር፣ በንጉሠ ነገሥትም መንግሥት ሆነ በደርጉ ዘመን ቢሆንም ይታይ ነበር።