ከ«ጥቅምት ፳፫» ለውጦች መካከል ያለው ልዩነት
Content deleted Content added
No edit summary |
|||
መስመር፡ 22፦ | መስመር፡ 22፦ | ||
==ዋቢ ምንጮች== |
==ዋቢ ምንጮች== |
||
http://www.nytimes.com/learning/general/onthisday/20081102.html |
*http://www.nytimes.com/learning/general/onthisday/20081102.html |
||
<references/> |
<references/> |
||
[[መደብ:ዕለታት]] |
እትም በ14:34, 7 ሜይ 2010
ጥቅምት ፳፫ ቀን በኢትዮጵያ ዘመን አቆጣጠር የዓመቱ ፶፫ኛ ቀን ነው። ከዚህ ቀን በኋላ እስከ ዓመቱ መጨረሻ ድረስ፣ በ ዘመነ ሉቃስ ፫፻፲፫ ቀናት በ ዘመነ ዮሐንስ፤ በ ዘመነ ማቴዎስ፤ እና በ ዘመነ ማርቆስ ደግሞ ፫፻፲፪ ቀናት ይቀራሉ።
የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን ይሄንን ዕለት በየወሩ የሰማዕቱ ቅዱስ ጊዮርጊስ መታሰቢያ ቀን አድርጋዋለች።
ዓቢይ ታሪካዊ ማስታወሻዎች
፲፱፻፯ ዓ.ም. በአንደኛው የዓለም ጦርነት ሩሲያ በኦቶማን ንጉዛት ላይ ጦርነት አወጀች።
፲፱፻፳፫ ዓ.ም. በኢትዮጵያ፣ ንግሥተ ነገሥታት ዘውዲቱ በድንገተኛ ሞት ከአለፉ በኋላ አልጋ ወራሹ ንጉሥ ተፈሪ መኮንን ተተክተው በመናገሻ ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤተ ክርስቲያን የንጉሠ ነገሥትነት ዘውድ ጭነው ቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ ተባሉ።
፲፱፻፶፯ዓ.ም. በሳውዲ አረብያ ንጉዛት[1] ንጉሥ ሳውድ በቤተሰቦቻቸው ሽምቅ ከዙፋናቸው ተፈንቅለው በግማሽ ወንድማቸው በንጉሥ ፋይሳል ተተኩ።
፲፱፻፸፮ ዓ.ም. የአሜሪካው ፕሬዚደንት ሮናልድ ሬጋን በየዓመቱ የማርቲን ሉተር ኪንግ መታሰቢያ ቀን እንዲከበር የሚያስችለውን ብሔራዊ ህግ ፈረሙ።
፳፻ ዓ.ም. በሰሜን ሸዋ አስተዳደር፣ በኮረማሽ ወረዳ የሚገኘው የየለጥ ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤተ ክርስቲያን በዘማናዊ መልክ ከተገነባ በኋላ ተመርቆ አገልግሎት ላይ ዋለ።
ልደት
ዕለተ ሞት
ዋቢ ምንጮች
- ^ ንጉሥ እና ግዛት የሚሉትን ቃላት በማጣመር kingdom የሚለውን ቃል በአማርኛ ለመተርጎም የተፈጠረ