ሀይሉ ዲሣሣ
ሀይሉ ዲሣሣ ታዋቂ ኢትዮጵያዊ የኦሮምኛ ድምፃዊ፣ የግጥምና ዜማ ደራሲ እና ተዋናይ ነው።
የህይወት ታሪክ[ለማስተካከል | ኮድ አርም]
ሀይሉ ዲሣሣ በ፲፱፻፵፯ ዓ.ም. በወለጋ ክፍለ ሀገር ልዩ ስሙ ዳሌ ዳርቦ ጃሮ ቱሉ ሰዓ በሚባለው በቄለም አውራጃ በደምቢ ዶሎ ከተማ ተወለደ።
ሀይሉ ዲሣሣ በ፲፱፻፷፮ ዓ.ም. በሀገር ፍቅር ቲያትር በመቀጠር የኦሮምኛ ግጥምና ዜማን በመድረስ የተለያዩ ባህላዊና ዘመናዊ ዜማዎችን ተጫውቷል። ከዚህ በተጨማሪም በተለያዩ ድራማዎች ላይ በተዋናይነት ተሳትፏል። በተቀጠረበት በሀገር ፍቅር ቲያትር ቤትም በማገልገል ላይ ይገኛል።
የሥራዎች ዝርዝር[ለማስተካከል | ኮድ አርም]
ሀይሉ ዲሣሣ ሰባት የተለያዩ የኦሮምኛ ካሴቶችን አሳትሟል።
ማጣቀሻ[ለማስተካከል | ኮድ አርም]
- ናሽናል ቢብሊዮግራፊ ቡድን፣ የአንጋፋ አርቲስቶች መዝገበ የሕይወት ታሪክ፣ መጋቢት ፳፻፣ ገጽ 20 Archived ሴፕቴምበር 29, 2011 at the Wayback Machine