ራያ

ከውክፔዲያ
ዘልለው ለመሔድ፦ የማውጫ ቁልፎች, ፍለጋ

ራያ ማለት በስሜን ወሎ እና በደቡብ ትግራይ ሰፍሮ የሚገኝ ህዝብ ነው። ይህ ህዝብ የራሱ የሆነ ባህል እና ወግ፡ ማለትም እንደ አነጋገር፡ አለባበስ፡ የሰርግ ፡ የለቅሶ ስነስራአት ያለው ኩሩ እና ጀግና ህዝብ ነው። የራያ ህዝብ ከሚደነቅበትና ከሚያስደስት ባህሉ ሁሉም የእምነት ተከታዮች በተለይምሙስሊም ክርስቲያንሳይል በመቻቻል በህብረት በአንድ ላይ ተከባበሮ የሚኖር ህዝብ ሲሆን የአለባበስ ባህሉ ሌላው የሚደነቅለት አና ባህላዊ ጭፈራው ሲያዩት የሚያስግርም አና የሚያስድስት ነው። ከባህላዊ ጭፈራዎቹ እንደ "ጉማየ" "መጋልዋ" ፡ ወዘተ መጥቀስ ይቻላል፡፡ ህዝቡ የሚኖርበት አከባቢ እንደሚከተለው ይዋሰናል። በሰሜን እንደርታ፡ በደቡብ የጁ፡ በምስራቅ አፋር እንድሁም በምእራብ ላስታ ያዋሱኑታል። የከተሞች ስም ለመጥቀስ ያክል አላማጣቆቦኮረምማይጨውመሆኒ በመባል ይታወቃሉ። የህዝቡ አስተዳድር እንደየ መንግስቶቹ ስቀያየር የኖረ ሲሆን፡ ቀደም ስል ራያን በሁለት አውራጃዎች በመክፈል ራያ ና ቆቦ ማእከሉ አላማጣራያ ና አዘቦ ማእከሉ ማይጨው በማድረግ በወሎ ጠቅላይ ግዛት ስር ይተዳድር ነበር። በአሁን ስአት የወያኔ መንግስት በሚያራምድው የከፋፍለህ ግዛ ስርአት ሳይፈልግ፡ አዘቦን ሙሉ በሙሉ እንዲሁም ራያ ና ቆቦ በመባል ሲታወቅ የነብረዉን ለሁለት በመክፈል አላማጣን ወደ ትግራይ በመውሰድ የህዝቡን በተለይም የገበሬውን ኑሮ በማመሳቀል ላይ ይገኛል።

የኔ መሣርያዎች

Variants
Actions
የማውጫ ቁልፎች
ጠቃሚ መሣሪያዎች