አብርሃም

ከውክፔዲያ
ዘልለው ለመሔድ፦ የማውጫ ቁልፎች, ፍለጋ

አብርሃምመጽሐፍ ቅዱስ መሠረት በዑር ከላውዴዎን አብራም ተወልዶ በኋላ ወደ ካራንና ወደ ከነዓን ግብፅም የሄደው የዕብራውያን፣ የእስማኤላውያንና የብዙ ሕዝቦች አባት ነበረ።

የአብርሃም ታሪክ በተለይ የሚታወቀው ከብሉይ ኪዳን ኦሪት ዘፍጥረት ነው። በተጨማሪ መጽሐፈ ኩፋሌ ስለ አብርሃም ሕይወት ብዙ ምዕራፍ ይሰጣል።

የአብርሃም ዕድሜ በመጽሐፈ ኩፋሌ [ለማስተካከል]

  • 1876 ዓመተ ዓለም (ዓ.ዓ.) - አብራም ለአባቱ ታራ እና ለእናቱ ኤድና በዑር ከላውዴዎን ተወለደ።
  • 1891 ዓ.ዓ. - አብራም ወጣት ሆኖ በከብት የሚስብ ማረሻ ፈጠረ።
  • 1897 ዓ.ዓ. - ሦራ (በኋላ ሣራ) ተወለደች።
  • 1903 ዓ.ዓ. - አብራም አባቱን ታራን በጣኦታት ለምን ታምናለህ ብሎ ጠየቀው።
  • 1925 ዓ.ዓ. - አብራም ሦራንን አገባት።
  • 1932 ዓ.ዓ. - ሎጥ ተወለደ።
  • 1936 ዓ.ዓ. - አብራም የዑርን አረመኔ መቅደስ አቃጠለና ወደ ካራን ሸሸ።
  • 1950 ዓ.ዓ. - የሰናዖር ንጉሥ አምራፌልና የኤላም ንጉሥ ኮሎዶጎምርሰዶምን አካባቢ በከነዓን ያዙ።
  • 1951 ዓ.ዓ. - እግዚአብሔር አብርሃምን ባረከው፣ አብርሃምም ሰማያዊ ቋንቋ ለመማር ጀመረ።
  • 1953 ዓ.ዓ. - አብርሃም ከካራን ወደ ከነዓን ተጓዛ።
  • 1954 ዓ.ዓ. - ኬብሮን በከነዓን ተሠራ።
  • 1956 ዓ.ዓ. - አብርሃም ወደ ግብፅ ሄደ።
  • 1961 ዓ.ዓ. - ጣይናስ በግብጽ ተሠራ።
  • 1963 ዓ.ዓ. - አብርሃም ወደ ከነዓን ወደ ቤቴል ተመለሰ። ሰዶም በኤላም ላይ አመጸ።
  • 1964 ዓ.ዓ. - የነገስታት ጦርነት፦ የአብርሃም ሠራዊት አምራፌልን ወዘተ. አሸነፉ።
  • 1965 ዓ.ዓ. - እስማኤል ተወለደ።
  • 1979 ዓ.ዓ. - እሳት ከሰማይ ሰዶምንና ገሞራን አጠፋ። አብርሃም ወደ ቤርሳቤ ሄደ፣ ይስሐቅ ተወለደ።
  • 1982 ዓ.ዓ. - እስማኤልና እናቱ ሀጋር ወደ ፓራን ተሰደዱ።
  • 2003 ዓ.ዓ. - አብርሃምና ይስሐቅ ወደ ደብረ ጽዮን ተጓዙ፤ ወደ ቤርሳቤ ተመለሱ።
  • 2010 ዓ.ዓ. - አብርሃም ከቤርሳቤ ወደ ኬብሮን ተመለሰ።
  • 2024 ዓ.ዓ. - ሣራ ዐረፈች፤ ለመቃበርዋም አብርሃም ዋሻ ከኬጢያውያን ሰው ከኤፍሮን ገዛ።
  • 2027 ዓ.ዓ. - ይስሐቅ ርብቃን አገባት።
  • 2046 ዓ.ዓ. - ያዕቆብኤሳው ለይስሐቅ ተወለዱ።
  • 2060 ዓ.ዓ. - አብርሃም አረፈ።