ኣጣርድ

ከውክፔዲያ
ዘልለው ለመሔድ፦ የማውጫ ቁልፎች, ፍለጋ

ኣጣርድ ወይም ሜርኩሪመሬት በምትገኝበት ማለትም ሚልክ ዌይ ተብሎ በሚጠራው ረጨት ወይም የከዋክብት ስብስብ ውስጥ የሚገኝ ፕላኔት ነው። ይህ ፕላኔት ከፀሐይ ባለው ርቀት ቅርቡ (1ኛው) ነው። ከበስተኋላው ዘጠኙም ፕላኔቶች ማለትም ቬነስመሬትማርስጁፒተርሳተርን ኡራኑስነፕቲዩን እና ፕሉቶ ይገኛሉ።

Mercury in color - Prockter07 centered.jpeg

ስሙ «ኣጣርድ» የተወረደ ከአረብኛው «ኡጣሪድ» ነበር። በድሮ ጊዜ ይህ የአረመኔ ጣዖት ስም ነበር። አሕዛብ ይህ የጥበብ ጣኦት እንደ ነበር ስላመኑ፣ የፈለኩ ስም ከዚህ ጣኦት ስም መጥቶ በየቋንቋው ይለያይ ነበር። ስለዚህ የፈለክም ሆነ የጣኦት ስም በፋርስኛ «ቲር»፣ በባቢሎንኛ «ናቡ»፣ በጥንታዊ እንግሊዝኛ «ዎደን»፣ በግሪክ «ሄርሜስ»፣ በሮማይስጥም «ሜርኩሪዩስ» ሆነ። «ሜርኩሪ» የሚለው እንግሊዝኛ ሲሆን ከዚሁ ሮማይስጥ ስም መጣ። በዕብራይስጥ ግን ስሙ «ኮካብ ሐማህ» ወይም «የፀሐይ ኮከብ» ይባላል።

[ለማስተካከል] ይዘት

ይህ ፕላኔት በዚህ ረጨት ውስጥ ከሚገኙ ፕላኔቶች በመጠኑ ትንሹ ነው። ዲያሜትሩ 2439.7 ኪ.ሜ ብቻ ነው። መዋቅሩ ከመሬት ጋር በተመሳሳይ ሁኔታ ቋጥኞች የበዙበት ነው።