ካርል ማርክስ
ካርል ሔንሪክ ማርክስ (ግንቦት 5, 1818 – መጋቢት 14, 1883) ጀርመናዊ ፈላስፋ እና የፖለቲካ ተመራማሪ ነበር። የካርል ማርክስ ፅሑፎች በገንዘብ( ኢኮኖሚ) እና የኅይል ፖለቲካ ላይ ያተኮሩ ነበር። በማርክስ አስተሳስብ ደመወዝ ተከፋይ ጉልበት ባለበት ሁሉ የመደብ ትግል ይኖራል ብሎ ያምን ነበር። በእርሱ እመነት ይህ የመደብ ትግል በሰራተኞች አሸናፊነትና የበላይነት የሚደመደም ነው።
ከካርል ማርክስ መጻሕፍት ውስጥ ኮሚዩኒስት ማኒፌስቶ የተሰኘው መጽሃፉ በጣም ታዋቂው ሲሆን ከፍሬድሪክ ኤንግልስ ጋር አብሮ በ1840ዓ.ም. የደረሰው ነበር። መጽሐፉ የኮሚዩኒዝምን ሃሳቦችና አላማወች ለማስቀመጥ ይጥራል። እኒህ ሃሳቦቹ በአሁኑ ዘመን ማርክሲዝም በመባል ይታወቃሉ።
በሌላ ጎን ካርል ማርክስ ከደረሳቸው መጻሕፍት ዳስ ካፒታል የሚሰኘው እንደ ዋና ስራው ተደርጎ ይወሰዳል። የዚህ መጽሐፉ ሦስት ክፍሎች ብዙ ጊዜውን እንደወሰዱ ይነገራል። ዳስ ካፒታል እንዴት ካፒታሊዝም እንደሚሰራ ሲገልጽ በዚያው ልክ ካፒታሊዝም የሚፈጥራቸውን ችግሮች አብሮ ያብራራል። የማርክስ ርዕዮተ አለም ለሶሻሊዝም መነሳትና ለሩሲያ አብዮት መንስኤ እንደሆነ በብዙዎች የታመነ ነው።
የማርክስ ታዋቂ ርዕዮት አለም ቁስ አካላዊነት ሲሆን፣ ሃይማኖት፣ ሥነ ምግባር እና ማህበረሰባዊ መዋቅሮች በሙሉ መሰረታቸው ኢኮኖሚክስ ነው ብሎ ያምን ነበር።
ብዙ ሰዎች እስካሁን ደረስ የማርክስን ሃሳብ ይከተላሉ፣ እንዲሁም በማሳደግ ሲያዳብሩት ይታያሉ።
|
«ስግብግብ ያበደ ካፒታሊስት ሲሆን |
| — ካርል ማርክስ |