ዋርካ (ድረገጽ)

ከውክፔዲያ
ዘልለው ለመሔድ፦ የማውጫ ቁልፎች, ፍለጋ

ዋርካ ሳይበር ኢትዮጵያ በመባል የሚታወቀው ድኅረ ገጽ የአማርኛ ቋንቋ የውይይት መድረክ ድረ ገጽ ነው። ይህ ድኅረገጽ ኢትዮጵያውያን በራሳቸው ፊደል ለመወያየት ይችሉ ዘንድ በሁለት ወንድማማች ኢትዮጵያዊያን በሰኔ 1992ተፈጥሮ ዛሬ ሁሉንም ኢትዮጵያዊያን በስፋት እያገለገለ ያለ ዌብሳይት ሆኖአል።

ይሁን እንጂ ኅረ ገጹ እንደሚለው ከግንቦት 1998 ጀምሮ [1] ፥ የኢትዮጵያ መንግሥት ድረገጽን ስለአገደው በአገር ውስጥ እንዳይሰራ ወይም እንዳይታይ አግዷል። ሆኖም የአገር ውስጥ ጉዳይ ሚኒስትር አቶ ብርሃኑ ሃይሉ ስዋርካ/ሳይበር ኢትዮጵያና ስለሌሎቹም ስለታገዱ ፖለቲካ ነክ ድህረ ገጾች ጉዳይ ተጠይቀው ምንም የተከለከለ ህረገጽ የለም የማይታዩበት ምክንያትም አይታወቅም በማለት በተደጋጋሚ አስተባብለዋል። ዋርካ ወይም ሳይበር ኢትዮጵያ በምዕራቡና በዓለም ዙሪያ ለሚኖረው ኢትዮጵያዊያን ሕብረተሰብ በማህበራዊ ፡በኢኮኖሚያዊ ወይም የዕለት ከዕለት ኑሮ ስለ ፖለቲካ ወይም ስለ ባሕል እና ስነ-ጽሑፍ፣ ስነ-ጥበብ ፤ ኪነ-ጥበብ ፤ ፍቅር ፡ሃይማኖት እንዲሁም ወቅታዊ ጉዳዮችን ሊያወያዩ የሚችሉ በጣም ጠቃሚ መድረኮች ስላሉት መፍትሔ ያጡለትን ጉዳዮች በውይይት መፍትሔ እንደዳስገኘለት ከተጠቃሚዎች የተገኘ መረጃ ያረጋግጣል።

የውጭ መያያዣ [ለማስተካከል]