ውክፔዲያ:ታሪካዊ ማስታወሻዎች/ኅዳር 20

ከውክፔዲያ

ኅዳር ፳

  • ፲፯፻፸፬ ዓ.ም. በሊቨርፑልብሪታንያ ከተማ የተመዘገበ የአፍሪቃ ሰዎችን በግዳጅ ለአገልግሎት የሚሸጥ ድርጅት ንብረት የነበረችው “ዞንግ” የምትባለው መርከብ ከጫነቻቸው ሰዎች መቶ ሠላሳ ሦሥቱን አፍሪቃውያኖች መርከበኞቹ በሕይወት እያሉ ወደ ባሕር ጥለው ገደሏቸው። በአሥራ ስምንተኛው ክፍለ ዘመን ለባርነት የሚጫኑ የአፍሪቃ ዜጎች በአውሮፓ ሕግ ፊት እንደ ዕቃ ንብረት እንጂ እንደ ሰው ስለማይቆጠሩ፣ ይሄንን ታላቅ ወንጀል የፈጸሙት ሰዎች አልተከሰሱም። የመርከቧ ባለቤቶች ግን “ለጠፋው ንብረት’’ የዋስትና ውል የሰጣቸውን ድርጅት በፍርድ ቤት የኪሳራቸውን ዋጋ እንዲከፍላቸው ክስ አቀረቡ።
  • ፲፱፻፵ ዓ.ም. የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ፍልስጥኤምን በሐይማኖት መሠረት ለሁለት ከፍሎ አንደኛው የይሁዳዊ መንግሥት፤ ሁለተኛውን ክፍል ደግሞ የአረብ መንግሥት እንዲመሠረት የሚያስችለውን “ውሳኔ ፻፹፩” አጸደቀ። ይሄው ውሳኔ በድምጽ ሠላሣ ሦስት አገሮች ሲደግፉት፤ አሥራ ሦሥት አገሮች ተቃውመው አሥር አገሮች ደግሞ የድጋፍም የቅራኔም ድምጽ ከመስጠት ተቆጥበዋል። ኢትዮጵያ እና ብሪታንያ ከነኝህ ከአሥር አገሮች መሀል ይገኛሉ።<