የ፷ዎቹ መኮንኖች ግድያ

ከውክፔዲያ
ዘልለው ለመሔድ፦ የማውጫ ቁልፎች, ፍለጋ
የ፷ዎቹ መኮንኖች ግድያ ውሳኔ

ደርግ ከፍተኛ ባለሥልጣናት ቀጥተኛ ትዕዛዝ በአጠቃላይ ፷ የቀድሞው የዘውድ ሥርዓት ባለሥልጣናት በአንድ ላይ ያለፍርድ፣ በኅዳር 1967 ዓ.ም. ተገደሉ። እስከዚህ ድርጊት ድረስ ከየካቲት ፲፱፻፷፮ ዓ/ም ጀምሮ ያለደም ማፍሰስ ሲካሄድ የቆየውና በመስከረም ወር የቀድሞውን የዘውድ ሥርዓት ያለአንዳችም ሽብር ከሥልጣን ያወረደው አብዮት ከዚህ ኢሰብዓዊ አድራጎት በኋላ እስከ ዕድሜው ፍጻሜ ድረስ በደም የተጨማለቀ አድርጎታል።