ደደሆ
ደደሆ (Euclea racemosa) ኢትዮጵያ ውስጥ የሚገኝ ተክል ነው።
የተክሉ ሳይንሳዊ ጸባይ[ለማስተካከል | ኮድ አርም]
ሁሌ ለም ዛፍ ወይም ቊጥቋጥ አይነት ነው። ብዙ ቅጠላቅጠልና ትንንሽ ቀይ፣ ሐምራዊና ጥቁር ፍሬዎች አሉበት።
በአፋርኛና በሶማልኛ የሌላ ዝርያ ዛፍ Salvadora persica «ደደሆ» ይባላል፤ የዚያው ዛፍ ስም በአማርኛ መሮ ነው።
አስተዳደግ[ለማስተካከል | ኮድ አርም]
በብዛት የሚገኝበት መልክዓ ምድር[ለማስተካከል | ኮድ አርም]
በኮረብቶች ወይም በእዳሪ መሬት ተራ ነው።
በምስራቃዊው አፍሪካ ከግብጽ እስከ ደቡብ አፍሪካ ድረስ፣ እንዲሁም በኮሞሮስ፣ በኦማንና በየመን ይገኛል።
የተክሉ ጥቅም[ለማስተካከል | ኮድ አርም]
ትንንሽ ፈሬዎቹ ሊበሉ ይቻላል፤ በትልቅ መጠን ቢበላ ግን የሆድ ማበጥ ያደርጋል። ፍሬዎቹም በአዕዋፍ ይበላሉ።
ፍሬዎቹም «የደደሆ ኮምጣጤ» ለመሥራት ይጠቀማሉ።
ጥቁር ፍሬዎቹ ደግሞ ሐምራዊ ቀለም ለመሥራት ይጠቀማሉ።[1]
በፍቼ በተደረገ ጥናት ዘንድ፣ የደደሆ ቅጠል ዱቄት ለጥፍ ለኪንታሮት ይለጠፋል። የቅጠሉ ጭማቂም ለኮሶ ትል ወይንም ለአባለዘር በሽታ ይጠጣል። አገዳውም ለጥርስ ሕመም ይኘካል።[2]
ጅምር! ይህ አጭር ጽሑፍ መሠረት ወይም መዋቅር ነው። አሁን ሊያስፋፉት ይችላሉ! |
- ^ አማራ ጌታሁን - SOME COMMON MEDICINAL AND POISONOUS PLANTS USED IN ETHIOPIAN FOLK MEDICINE Archived ጁላይ 31, 2017 at the Wayback Machine March 1976 እ.ኤ.አ.
- ^ የፍቼ፣ ኦሮሚያ ባህላዊ መድሃኒት ጥናት 2006 ዓም ከዓቢዩ እኒየው እና ሌሎች፣ ጎንደርና አዲስ አበባ ኡኒቨርሲቲዎች ሥነ ፍጥረት ኮሌጆች