ሄክታር

ከውክፔዲያ

ሄክታር የአለም አቀፍ ክልል መለኪያ ሲሆን፣ ትርጉሙ በየጎኑ አንድ መቶ ሜትር ያለው ካሬ (አራት ማዕዘን ያለው) ክልል ስፋት ማለት ነው።

ቃሉ (በፈረንሳይኛ በኩል) የደረሰው ከግሪክኛ ἑκατόν /ሄካቶን/ «መቶ»፣ እና ሮማይስጥ area /አሬያ/ «ክልል» ነበር።

ሄክታር ስለዚህ አሥር ሺህ ካሬ ሜትር አለበት። ሄክታር በተለይ ለመሬት (ርስት ወይም እርሻ) ክልል ለመለካት ይጠቀማል።