ሎሜ

ከውክፔዲያ

ሎሜ (Lomé) የቶጎ ዋና ከተማ ነው።

ከተማው በ18ኛ ክፍለ-ዘመን በኤዌ ሕዝብ ተመሠረተ። ያንግዜ ስሙ 'በይ ቢች' ነበር። በ1889 ዓ.ም. ጀርመኖች የመንግሥት መቀመጫ ወዲህ ከአኔሆ አዛወሩት። በ1907 ዓ.ም. በ1ኛ ዓለማዊ ጦርነት መጀመርያ ፈረንሳዮች ያዙት።

የሚኖርበት የህዝብ ቁጥር ከነ አካባቢው 749,700 ሆኖ ሲገመት ከተማ ብቻውን 676,400 ሰዎች አሉበት። ከተማው 06°10′ ሰሜን ኬክሮስ እና 01°21′ ምሥራቅ ኬንትሮስ ላይ ተቀምጦ ይገኛል።