Jump to content

መሀመድ ሁሴን አሊ አላሙዲ

ከውክፔዲያ
የንግድ ሰው መረጃ
መረጃአካል
ስም ሼህ መሀመድ ሁሴን አሊ አላሙዲ
የትውልድ ቀን 1946
የትውልድ ቦታ ደሴ
ዜግነት የሳውዲ አረቢያ እና ኢትዮጵያ ጥምር ዜግነት
ድርጅቶች ሚድሮክ ኢትዮጵያ የቴክኖሎጂ ግሩፕ
የትምህርት ደረጃ
የስራ ዓይነት በሆቴል እና በተለያዩ የንግድ እና የኢንዱስትሪ ዘርፎች ኢንቨስት
የዓመት ገቢ
የሰራተኞች ብዛት
ድህረ ገፅ [ መግቢያ]

ዶ/ር ሼህ መሀመድ ሁሴን አሊ አላሙዲ1946 እ.አ.አ. ኢትዮጵያ ውስጥ በደሴ ከተማ ተወለዱ። እኚህ ግለሰብ ያደጉት በወልድያ ከተማ ሲሆን የሳውዲ አረቢያ እና ኢትዮጵያ ጥምር ዜግነት ያላቸው ታዋቂ ባለሃብት ናቸው። ፎርብስ ድረ ገጽ በ2009/10 እ.አ.አ. ባወጣው መረጃ መሰረት በ10 ቢሊዮን ዶላር የአለማችን 94ኛ ባለሃብትም ናቸው። ካላቸው ሃብት ከ3 ቢሊዮን ዶላር በላይ በኢትዮጵያ ውስጥ በሆቴል እና በተለያዩ የንግድ እና የኢንዱስትሪ ዘርፎች ኢንቨስት ያደረጉ ሲሆን ዋነኛው የገቢ ምንጫቸው በተለያዩ ሃገራት የተቋቋሙት የፔትሮሊየም ነዳጅ ዘይት ማምረቻዎች ናቸው።

ባለሃብቱ በኢትዮጵያ ውስጥ ከሃያ በላይ እህት ድርጅቶችን ያቀፈው የሚድሮክ ኢትዮጵያ የቴክኖሎጂ ግሩፕ ባለቤትና ሊቀመንበር ናቸው። በጤና ምክንያት ለተቸገሩ ታዋቂ ኢትዮጵያውያን እርዳታ በመለገስ ይታወቃሉ።