መሀመድ ሁሴን አሊ አላሙዲ
Appearance
| መረጃ | አካል |
|---|---|
| ስም | ሼህ መሀመድ ሁሴን አሊ አላሙዲ |
| የትውልድ ቀን | 1946 |
| የትውልድ ቦታ | ደሴ |
| ዜግነት | የሳውዲ አረቢያ እና ኢትዮጵያ ጥምር ዜግነት |
| ድርጅቶች | ሚድሮክ ኢትዮጵያ የቴክኖሎጂ ግሩፕ |
| የትምህርት ደረጃ | |
| የስራ ዓይነት | በሆቴል እና በተለያዩ የንግድ እና የኢንዱስትሪ ዘርፎች ኢንቨስት |
| የዓመት ገቢ | |
| የሰራተኞች ብዛት | |
| ድህረ ገፅ | [ መግቢያ] |
ዶ/ር ሼህ መሀመድ ሁሴን አሊ አላሙዲ በ1946 እ.አ.አ. ኢትዮጵያ ውስጥ በደሴ ከተማ ተወለዱ። እኚህ ግለሰብ ያደጉት በወልድያ ከተማ ሲሆን የሳውዲ አረቢያ እና ኢትዮጵያ ጥምር ዜግነት ያላቸው ታዋቂ ባለሃብት ናቸው። ፎርብስ ድረ ገጽ በ2009/10 እ.አ.አ. ባወጣው መረጃ መሰረት በ10 ቢሊዮን ዶላር የአለማችን 94ኛ ባለሃብትም ናቸው። ካላቸው ሃብት ከ3 ቢሊዮን ዶላር በላይ በኢትዮጵያ ውስጥ በሆቴል እና በተለያዩ የንግድ እና የኢንዱስትሪ ዘርፎች ኢንቨስት ያደረጉ ሲሆን ዋነኛው የገቢ ምንጫቸው በተለያዩ ሃገራት የተቋቋሙት የፔትሮሊየም ነዳጅ ዘይት ማምረቻዎች ናቸው።
ባለሃብቱ በኢትዮጵያ ውስጥ ከሃያ በላይ እህት ድርጅቶችን ያቀፈው የሚድሮክ ኢትዮጵያ የቴክኖሎጂ ግሩፕ ባለቤትና ሊቀመንበር ናቸው። በጤና ምክንያት ለተቸገሩ ታዋቂ ኢትዮጵያውያን እርዳታ በመለገስ ይታወቃሉ።