ማናማ

ከውክፔዲያ

ማናማ (አረብኛ፡ المنامة) የባህሬን ዋና ከተማ ነው። የሚኖርበት የህዝብ ቁጥር የአካባቢውን ኗሪ ሲጨምር 527,000 ሆኖ ሲገመት የራሱ የከተማው ኗሪ ቁጥር ደግሞ 149,900 ሆኖ ይገመታል። ከተማው 26°12′ ሰሜን ኬክሮስ እና 50°38′ ምሥራቅ ኬንትሮስ ላይ ተቀምጦ ይገኛል። ማናማ ቢያንስ ቢያንስ ከ1337 ዓ.ም. በፊት ነበረ። በ1513 ዓ.ም. ፖርቱጋል ያዘውና በ1594 ዓ.ም. ፋርስ ያዘው።