ማድሪድ

ከውክፔዲያ

ማድሪድ (Madrid) የእስፓንያ ዋና ከተማ ነው።

ስሙ በሮማይስጥ (/ማትሪኬ/) ሆኖ ከ2ኛው ክፍለ ዘመን ጀምሮ ይታወቃል። በ1553 ዓ.ም. የእስፓንያ መንግሥት ግቢ ከቫያዶሊድ ወደ ማድሪድ ተዛወረ።

የሚኖርበት የህዝብ ቁጥር የአካባቢውን ኗሪ ሲጨምር 8,561,748 ሆኖ ሲገመት የራሱ የከተማው ኗሪ ቁጥር ደግሞ 3,228,359 ሆኖ ይገመታል። ከተማው 40°25′ ሰሜን ኬክሮስ እና 03°43′ ምዕራብ ኬንትሮስ ላይ ተቀምጦ ይገኛል።