ሜክሲኮ ከተማ

ከውክፔዲያ

ሜክሲኮ ከተማ (እስፓንኛCiudad de México /ሲዩዳድ ዴ ሜሒኮ/) የሜክሲኮ ዋና ከተማ ነው። ከተማው ቴኖችቲትላን ተብሎ የተመሠረተው በመጋቢት 14 ቀን 1317 ዓ.ም. በአዝቴክ (መሺካ) ኗሪዎች ነበር።

ቶሬ ማዮር ከቻፑልቴፔክ ቤተ መንግስት ሲታይ

የሚኖርበት የህዝብ ቁጥር የአካባቢውን ኗሪ ሲጨምር 19,231,829 ሆኖ ሲገመት የራሱ የከተማው ኗሪ ቁጥር ደግሞ 8,720,916 ሆኖ ይገመታል። ከተማው 19°24′ ሰሜን ኬክሮስ እና 99°7′ ምዕራብ ኬንትሮስ ላይ ተቀምጦ ይገኛል።