ሥዮንግ-ኑ

ከውክፔዲያ
የሥዮንግኑ ምድር ስፋት 250 ዓክልበ. ግድም

ሥዮንግ-ኑ (ቻይንኛ፦ 匈奴) በጥንታዊ ሞንጎሊያ አካባቢ የተገኘ ብሔር ነበር። በተለይ በዚያ ስም ከ225 ዓክልበ. እና 400 ዓ.ም. መካከል በቻይና መዝገቦች በኩል ይታወቃሉ። ከዚህ በኋላ አውሮፓን የወረረው የሆኖች ብሔር ከሥዮንግኑ እንደ ወጡ ይመስላል።

በጠቅላላ ምንም ጽሕፈት ስላልነበራቸው መዝገቦች መጻፍ አልቻሉም ነበር። ሆኖም አለቆቹ በቻይና ጽሕፈት ወይም የኦርኾን ጽሕፈት በመሰለ ፊደል አይነት መልዕክት እንደ ጻፉ ተብሏል።