ሳህለወርቅ ዘውዴ

ከውክፔዲያ
ሳህለወርቅ ዘውዴ
የኢትዮጵያ ፕሬዝዳንት
ከጥቅምት ፲፭ ቀን ፳፻፲፩ ዓ.ም. ጀምሮ
ጠቅላይ ሚኒስትር ኣብይ ኣህመድ
ቀዳሚ ሙላቱ ተሾመ
የተወለዱት ፲፱፻፵፪ ዓ.ም.
አዲስ አበባኢትዮጵያ
ዜግነት ኢትዮጵያዊ
ሀይማኖት የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ክርስትና

አምባሳደር ሳህለወርቅ ዘውዴኢትዮጵያ የመጀመርያው ሴት ፕሬዚዳንት ናቸው።[1]

የህይወት ታሪክ እና ትምህርት[ለማስተካከል | ኮድ አርም]

አምባሳደር ሳህለወርቅ ዘውዴ በወርሃ የካቲት ፲፱፻፵፪ በአዲስ አበባ ከተማ ነው የተወለዱት። አምባሳደር ሳህለወርቅ ዘውዴ የመጀመርያ እና የሁለተኛ ደረጃ ትምርታቸውን ያጠናቀቁት በሊሴ ገብረማርያም ትምርት ቤት ነው። አምባሳደር ሳህለወርቅ የፈረንሳዩ ሞንተፔለ ዩኒቨርሲቲ የተፈጥሮ ሳይንስ ምሩቅ ናቸው። አማርኛፈረንሳይኛ፣ እና እንግሊዘኛ አቀላጥፈው ይናገራሉ አባታቸዉ ዘዉዴ ሰሜን ሽዋ ደራ ጉ/መስቀል ሲሆን ትዉልዳቸዉ እናታቸዉ ከጎጃም ማንኩሳ ምንም የዘርብሄር ድብልቅ ሳይሆኑ ፅድት ያሉ አማራዊት ናቸዉ ኢትዮጵያም ያማራ ነች ሌላዉ ስደተኛ ነዉ ዝክረ ታሪክ እንደሚገልጠዉ......

የስራ ዝርዝር[ለማስተካከል | ኮድ አርም]

የዲፕሎማት ስራቸው[ለማስተካከል | ኮድ አርም]

አምባሳደር ሳህለወርቅ ዘውዴ ለኢትዮፕያ እንደ ውጪ አገር አገልግሎት ሰራተኛ ብዙ አመታት አገልግለዋል። እኤአ ከ1989-1993 ተቀማጭነታቸውን ሴነጋል በማድረግ የማሊ፣ የኬፕ ቨርድ፣ የጊኒ ቢሳዎ፣ የጋምቢያና የጊኒ አምባሳደር በመሆን አገልግለዋል። እኤአ ከ1993-2002 ደግሞ በጅቡቲ አምባሳደር ሆነው የሰሩ ሲሆን በወቅቱ የምሥራቅ አፍሪካ የልማት በየነ መንግሥታት ድርጅት (ኢጋድ) ቋሚ ተወካይም ነበሩ።

ከዚያም በመቀጠል እኤአ ከ2002-2006 በፈረንሳይ አምባሳደር እንዲሁም የተባበሩት መንግሥታት የትምህርት የሳይንስና የባህል ተቋም ተወካይ ሆነው ሰርተዋል።

የተባበሩት መንግስታት ስራቸው[ለማስተካከል | ኮድ አርም]

በተባበሩት መንግሥታት ልዩ መልዕክተኛ ውስጥ የተቀናጀው የሰላም አስከባሪ ሃይል ተወካይ በመሆን በሴንትራል አፍሪካ(BINUCA) ኃላፊ በመሆን አገልግለዋል።

በአፍሪካ ሕብረት ውስጥና በተባበሩት መንግሥታት የኢኮኖሚ ኮሚሽን ውስጥም የኢትዮጵያ ቋሚ ተወካይ ሆነው ያገለገሉት አምባሳደር ሳህለወርቅ በውጪ ጉዳይ ሚኒስቴር ውስጥም የአፍሪካ ጉዳዮች ዳይሬክተር ጄነራል ሆነው ሰርተዋል።

እኤአ በ2011 የተባበሩት መንግሥታት ዋና ፀሃፊ የነበሩት ባን ኪሙንም በኬኒያ የተባበሩት መንግሥታት ዳይሬክተር ጄነራል አድርገው ሾመዋቸው አገልግለዋል።

በተባበሩት መንግሥታት ዋና ፀሃፊ አንቶኒዮ ጉቴሬስ በአፍሪካ ሕብረት ልዩ ተወካይ እንዲሁም በአፍሪካ ሕብረት የተባበሩት መንግሥታት ቢሮ ኃላፊ ሆነው ተሾመዋል።

ኢትዮጵያ ፕሬዝዳንት[ለማስተካከል | ኮድ አርም]

አምባሳደር ሳህለወርቅ ጥቅምት ፩፭ ቀን ፳፻፲፩ ዓ.ም. የኢትዮፕያ ፕሬዝዳንት ሆነው ተመርጡ። በፕሬዝዳንትነት ሚና ለማገልገል የመጀመርያዋ ሴት ሲሆኑ የኢትዮጵያ ሕዝቦች አብዮታዊ ዲሞክራሲያዊ ግንባር አራተኛ ፕሬዝዳንት ናቸው። አምባሳደር ሳህለወርቅ ሁለት የስድስት አመት ውል እንደሚያገለግሉ ይጠበቃል። በአሁኑ ጊዜ በአፍሪካ ውስጥ አምባሳደር ሳህለወርቅ ብቻ ናቸው ሴት የአገር መሪ። ከሳቸው በፊት ኢትዮፕያ አንድ ሌላ ሴት መሪ ኖርዋት ያውቃል፤ እሳቸውም ንግሥት ዘውዲቱ ናቸው።

ማጣቀሻወች[ለማስተካከል | ኮድ አርም]

  1. ^ "Ethiopia gets first female president". BBC (25 October 2018).