ውክፔዲያ:የመጣጥፍ አቀማመጥ ልምድ

ከውክፔዲያ
የውክፔዲያ መጣጥፍ አቀማመጥ ልምድን የሚያሳይ ስዕል

መጣጥፎች ይህን መሠረታዊ የአቀማመጥ ልምድ እንዲከተሉ ይመከራል። እነዚህ ልምዶች ለእርዳታና ለምክር የሚያገለግሉ እንጂ ጥብቅ የማይጣሱ ሕጎች አይደሉም።

የመጣጥፉ አርዕስት[ኮድ አርም]

አርዕስቱ ለመጀመሪያ ጊዜ በመጣጥፉ ውስጥ ሲጻፍ፣ በ''' ''' ውስጥ ይቀመጥ። ለምሳሌ፦

  • «ሻይ ከልዩ የሻይ ቁጥቋጦ...» ሳይሆን «ሻይ ከልዩ የሻይ ቁጥቋጦ...»

የመጀመሪያው ዓረፍተ-ነገር[ኮድ አርም]

የመጀመሪያው ዓረፍተ-ነገር ስለ መጣጥፉ አርዕስት መሠረታዊ መረጃ ሊሰጥ ይገባል። ለምሳሌ፦

  • ስለ ድመት ያለው መጣጥፍ እንዲህ ይጀምራል፤ «ድመት አንስተኛ ስጋ በሊታ እንስሳ ስትሆን እቤት ውስጥ አይጥና የመሳሰሉትን ተውሳኮች ለመያዝ ታገለግላቸ።»

ከሌላ ቋንቋ የመጡ ቃላት[ኮድ አርም]

የመጣጥፉ አርዕስት የአማርኛ ቃል ካልሆነ፣ በቅንፍ ውስጥ የመነጨበትን ቋንቋ፣ ከዚያም ቃሉ በዚያ ቋንቋ አፃፃፍ፣ በመጨረሻም የቃሉ አባባል በአማርኛ በህዝባር (/ /) ውስጥ ያኑሩ። ለምሳሌ፦

  • ሩሲያ (መስኮብኛРоссия /ሮሲያ/) ወይም የሩሲያ ፌዴሬሽን (መስኮብኛ፦ Российская Федерация /ሮሲስካያ ፍየድየራትሲያ/) በአውሮፓ እና እስያ አህጉሮች ውስጥ የምትገኝ አገር ናት።

የውጭ ቃል ሆነው በአማርኛው ተናጋሪ ዘንድ ተለማጅነት ያላቸው ነገር ግን ትርጉማቸው በጣም ረጅም የሚሆን ከሆነ፣ በውጭውና በተለመደው ቃል ጽሁፍወን ያቅርቡ

የመረጃ መለጠፊያዎች[ኮድ አርም]

የመረጃ መለጠፊያዎች (ለምሳሌ የሀገር መረጃ) በቀኝ በኩል ይቀመጡ።

ስዕሎች[ኮድ አርም]

  • አብዛኛው ጊዜ በጣም ሰፊ ቦታ በመጣጥፉ ውስጥ እንዳይዙ፣ ለስዕሎች thumb የሚለውን ትዕዛዝ ይጠቀሙ። ለምሳሌ፦
[[ስዕል:Queen Nzinga 1657.png|thumb]]
  • በአንድ መጣጥፍ ውስጥ ብዙ ስዕሎች ካሉ፤ አቀማመጣቸውን በግራና በቀኝ ይለውጡ። left የሚለው ትዕዛዝ በግራ በኩል ያስቀምጣል። right የሚለው ደግሞ (ወይም ምንም የአቅጣጫ ትዕዛዝ ከሌለ) በቀኝ በኩል ያስቀምጣል። ለምሳሌ፦
[[ስዕል:Queen Nzinga 1657.png|thumb]]
[[ስዕል:Edgar Allan Poe 2.jpg|thumb|left]]
  • ለስዕል መግለጫ ይስጡ። ለምሳሌ፦
[[ስዕል:Queen Nzinga 1657.png|thumb|left|ንግሥት ንዚንጋ ከሏንዳ አስተዳዳሪ ጋር የሰላም ስምምነት ስታደርግ፣ 1657 እ.ኤ.አ.]]

ምንጮች[ኮድ አርም]

የግርጌ ማስታወሻዎች (እንግሊዝኛ፡ footnotes)፣ ዋቢ ምንጮች፣ ለተጨማሪ መረጃ የሚያገለግሉ መጻሕፍትና የውጭ መያያዣዎች ከመጣጥፉ ይዘት መጨረሻ ላይ በራሳቸው ንዑስ ክፍል ያስቀምጡ። የእነዚህ ምንጮች ቋንቋ አማርኛ ካልሆነ በቅንፍ () ውስጥ ቋንቋው ምን እንደሆነ ይጠቁሙ።

السلام عليكم ورحمه الله وبركاته አህባሽ ማን ነው የሀበሺ (አህባሽ) መንገድ የጀመረው አብደላ አል-ሐረሪ የተባለ ግለሰብ ነበር፡፡ ግለሰቡ ሐረር የተወለደ ሲሆን የሀይለ ስላሴ መንግስት ቀኝ እጅ ነበር፡፡ ከሃይለስላሴ አማች አንደርጌ ጋር ሆኖ ዓሊሞችን ሲያሳስር፣ መብትና እኩልነትን የሚሉትን ሙስሊሞችን ሲያጠቃ እና ሲሰልል ቆየ፡፡እ.ኤ.አ በ1940 (1367 ሂጅራ) ላይ በሐረር የቁርኣን ሂፍዝ ማዕከል መምህራንን አሳስሮ መርከዙን አስዘጋ፡፡ የመርከዙን ዳይሬክተር ሼህ ኢብራሁም ሀሰንን አሳስሮ 23 ዓመታት አስረፈደባቸው፡፡ አብደላ አል-ሐረሪ የፈጠረው ፊትና ‹‹ፊትነተልኩሉብ›› ተብሎ ይታወቃል፡፡ ከዚያም ወደ አዲስ አበባ በመምጣት በሀደሬ ሰፈር ሙስሊሙን ሲያጋጭ ቆይቶ በ1948 ወደ እስራኤል ተጓዘ፡፡ ለዓመት በዚያ ቆይቶ በ1949 ወደ ሶሪያ ገባ፡፡ ከዚያም በ1950 ወደ ሊባኖስ ተጓዘ፡፡ በሊባኖስ ቁርአን በማቅራት ህፃናትን ማሳደን ቀጠለ፡፡ ቀስ እያለ በመቶዎች የሚቆጠሩ ተማሪች አፈራ፡፡ ከአገር ከወጣ በኋላ ከየሁዳዎች ጋር በሚስጢር ይገናኝ ጀመር። ከፍተኛ ገንዘብ ተመድቦለት እ.አ.አ በ1982 የሊባኖስ የርስ በርሱ ጦርነት ጊዜ ድምፁን አጥፍቶ ሀይሉን አጠናከረ፡፡ ከዚያ በ1980ዎች እስራኤል ሊባኖስ ስትወርና ስታጠቃ የሙስሊሞች ጀመዓ ስትወጋ አህባሾችን ግን ተወቻቸው፡፡ ምክንያቱም የርሷ ወዳጅ ናቸውና ነው፡፡ በ1990 አህባሾች በእስራኤል ተረድተው ወደ ፖለቲካ ገቡ፡፡ በ1992 የሊባኖስ ምርጫ ጥቂት ወንበር አሸንፈው ፓርላማ ገቡ፡፡ ቀስ በቀስ የራሳቸውን ሚሊሻ ጦር መለመሉ፡፡ ሙስሊሙን ማበጣበጡን ገፍተው ቀጠሉ፡፡ ከነርሱ ውጭ ያለውን ሁሉ ‹‹ካፊር›› እያሉ መፈረጁ ተያያዙት፡፡ ለመንግስትና ለእስራኤል መረጃ እየሰጡ ሙስሊሙን ማስመታት ጀመሩ፡፡ ራሳቸውን በውሸት ‹‹የሻፊዒ መዝሀብ እንከተላለን›› እያሉ ያስወራሉ፡፡ አህለል ሱንና ነው። አሻዓሪና ማቶረዲ ነን ይላሉ፡፡ ሱፊያም ነን ይላሉ። ሆኖም የሶፊያ ዓሊሞች በሊባኖስ በሌሎች ሀገራትም መጀመሪያ እውነት ሱፊያ ናቸው ብለው ተሸደውደው ነበር። ሆኖም በሗላ በዝርዝር ሲያውቋቸው አጋልጠው ምላሽ ጻፉባቸው። ሰዉም እንዲያውቃቸውን እና እናዳይከተሏቸው አስጠነቀቁ።እውነታው ግን እነርሱ የእስራኤል ቀኝ እጅ ናቸው፡፡ ቀሰ በቀስ አል-ሀበሺ የሱንና መንገድ እየበከለ ሺዓ፣ ሪፋኢ፣ ሙርጂአ፣ተክፊር፣ሱፊ፣አል-ጀበሪ፣ ቃዲሪያና ጃህሚያ ወዘተ መንገዶችን ቀይጦ(ስፕሪስሪስ) አድርጎ የራሱን አዲስ መንገድ ፈጠረ፡፡ የዓለም ሙስሊሞችን ማክፈር ያዘ፡፡ አብደላ አል-ሐረሪ ‹‹ሳዑዲ እንዴት ከፈረች?›› ብሎ ሁሉ መጽሀፍ ጽፏል፡፡ የነብዩ (ሶ.አ.ወ) አገር መካና መዲና የካፊር አገር ብሎ ጽፏል፡፡ ይህ ብቻ የየሁዳ መሳሪያ መሆኑን ቁልጭ አድርጎ ያሳያል፡፡ ለመሆኑ አቋማቸው ምንድነው? ቀጥሎ ጥቂቶችን ብቻ እናያለን፡- 1. ከካፊር ጋር ቁማር መጫወት፣ የካፊርን (ክርስቲያን) ጎረቤት መስረቅና ማጭበርበር ይቻላል ብሎ ያስተምራል።ዋናው እንዳይነቃ በድብቅ ማድረግና ዋናው መጠንቀቅ ነው ብሎ ያስተምራል፡፡ (መጽሐፉ ሰሪህ አል-በያን፣ገጽ 133) 2. ሰሀቦችን ይሳደባል፡፡ አንዳንዶቹን ሰሀቦች ካፊር ናቸው የጀሀነም ናቸው ብሎ ጽፏል፡፡ ለምሳሌ ታላቁን የነብዩ (ሶ.ዐ.ወ) ሆሃባ ሙአዊያ ኢብኑ አቢሱፍያን ካፊር የጀሀነም ሲል ገልጿል፡፡ የነብያችን (ሶ.ዐ.ወ) ባለቤት አዒሻን ተሳድቧል፡፡ 3. በነጃሳ መስገድ ይፈቀዳል ይላል፡፡(መጽሐፉ ቡግየቱ ጧሊብ፣ገጽ 99-100) 4. ዘካ የለም ይላል፡፡ ዘካ ከእስልምና ማዕዘናት አንዱ ነው፡፡ አህባሾች ግን ሰው ዘካ እንዳያወጣ ከወረቀቱ ብር(ኖት) ላይ ዘካ የለበትም ይላሉ፡፡ ይህ ማለት በባንክም ይሁን በቤትዎ ቢሊዮን ብር እንኳ ካለዎ ዘካ አይስጡ ብሎ ይቀሰቅሳሉ፡፡ 5. ሪባ (ወለድ) መውሰድን ያበረታታሉ፡፡ ባንክ ገንዝ አስቀምጠው ባንኩ የካፊሮች(ወይም ስራ አስኪያጁ ካፊር(ክርስቲያን) ከሆነ ጠላታችን ስለሆኑ ወለዱን መውሰድ ይቻላል ብለው ያስተምራሉ። 6. ሴቶቻቸው ሻሽ ብቻ አድርገው ሱሪ ማድረግ ይችላሉ ይላሉ። ጂንስና ፋሽንንም ያበረታታሉ፡፡ 7. በሊባኖስ አገር የሙዚቃ ባንድ አላቸው ይህ ባንዳቸው ‹‹James last›› ይባላል፡፡ ዓመታዊ የሙዚቃ ድግስ ያደርጋሉ:: በዛ ላይ ሴቶችና ወንዶች በጋራ ይጨፍራሉ፡፡ 8. የአጅነቢ ሴትን ፎቶ፣ ቪዲዮ አልያም በመስታወት ውስጥ ራቁቷን እንኳ ብትሆን በስሜትም ቢሆን ማየት ይቻላል:: ከቁርአንና ሱና ተቃራኒ ሆነው የተከለከለው በዓይን በቀጥታ ማየት ብቻ ነው ብለው ያስተምራሉ፡፡ 9. ‹‹ሪፋዒ›› የተሰኘ ጦሪቃን ያስፋፋሉ:: በኢትዮጵያ ጀምረዋል ይህ ጦሪቃ ከሺዓ ጋር የሚያመሳስለው ብዙ እምነት አለው፡፡ የኢትዮጵያ ሙስሊም ግን ሱኒ ነው፡፡ 10. እምነት በልብ ነው ባይሰግዱም ኢባዳ ባይሰራም አንዴ አመንኩ ማለት በቂ ነው ብለው ያስተምራሉ:: (መጽሀፍ አ-ደሊል አልቀዊም፣ ገጽ 7) 11. ተከታዮቻቸው በአሜሪካና ካናዳ የቂብላ አቅጣጫ ካልተቀየረ ብለው ረብሻ ፈጥረዋል፡፡ በመጨረሻም ከመስጊድ ሲባረሩ የራሳቸው መስጊድ በተለየ ቂብላ ላይ ሰሩ። አሁን ከሙስሊሙ በተለየ ቂብላ ነው መስጊዳቸው፡፡ 12. ድግምትን አይቃወሙም። ራሳቸውም ይፈፅማሉ፡፡ ለሲህር የሚጠቀሙበት ‹‹ሁቡብ አል-አሀብ›› ብለው የሚጠሩት ነገር አላቸው፡፡ 13. ቁርኣን የጂብሪል ቃል እንጂ የአላህ ቃል አይደለም ብለዋል። የአላህ ቃል አይፃፍም ይላሉ፡፡ 14. የሚገርመው ይህን ሁሉ የጥመት መንገድ እየተከተሉ ሱፊያ ነን፣ ሻፊዒ መዝሀብ ተከታይ ነን ይላሉ፡፡ 15. ከነርሱ እምነት ዉጭ ያሉ ዓሊሞችን እንደያስተምሩ ሆን ብለው ያስተጓጉላሉ፣ ይደበድባሉ፣ ያሳስራሉ፣ ያውካሉ፣ በአንድ ወቅት በሊባኖስ ይህ ችግር በስፋት ፈጥረው ‹‹ሸሪዓ መጽሔት›› በቁጥር 574 እትሙ ‹‹ሊባኖስ ጦርነት በመስጂዱ ውስጥ›› በሚል ርዕስ ጽሑፍ አስነበቦ ነበር፡፡ 16. ዓመታዊ የሴቶቻቸው የሂጃብ ፋሺን ሾው አላቸው፡፡ በዚያ ላይ ሂጃብ ከሚለብሱት ሴቶች ጋር በጋራ ይጨፍራሉ፡፡ የአህባሽ ስውር አጀንዳዎችPosted: October 9, 2011 in መግቢያ የአህባሽ ጉዳይ በኢትየጲያችን አነጋጋሪ አጀንዳ ከሆነ ሰንበትበት ብሏል ። በተለያዩ የመገናኛ ብዙሃንም ስለዚህ ጀመዓ ብዙ ብዙ ተብሏል ። አነጋጋሪነቱም ያለምክኒያት አይደለም ። ከአስተሣሠብ እስከ ሥነምግባር ፤ ከእምነት እስከ ማህበራዊ ኑሮ ግንኙነት በእጅጉ የወረደ አመለካከትና አስተምህሮ ያለው አህባሽ በህዝቡ መካከል ማረፊያ ቢያገኝ ሊያደርሰው የሚችለው ጥፋት ከፍተኛ ይሆናል የሚለው የብዙዎች ስጋት ነው ። አህባሽ እንከኖቹ ብዙ ናቸው ። ትኩረቱና መሠረቱ ከተውሂድ ይልቅ ወደ ሽርክ ( በአላህ ማጋራት ) እና ወደ ሸርክ የሚያደርሱ መንገዶች ያዘነበለ ነው ፤ ጥርት ካለው የቁርኣንና የሀዲስ ትምህርት በበለጠ ወደ ፍልስፍና እና መሠረት አልባ ቂሣዎች (ትረካዎች) ያደላል ፤ ከፍቅርና ከመደጋገፍ ይልቅ በማህበረሰቡ መካከል ጥላቻን ፣ ምቀኝነትንና ውጥረትን ያራምዳል ፤ ከሱ ውጭ ያሉትን ሁሉ የማክፈር (ከእስልምና የማስወጣት) ፖሊሲውና ‘ ለመቻቻል ወኔ የከዳው ስብስብ ’ መሆኑ ሲታሰብ ደግሞ የአህባሽ ጀመዓን አደገኛነትና የአስተሣሣቡን መርዛማነት አጉልቶ ያሣያል ። በመሆኑም ይህ ጉዳይ እጅግ አሣሣቢ ነው ስላመንበት በዛሬው የአጀንዳ አምዳችን የተለያዩ መረጃዎችን በማገላበጥ ስለዚህ ጀመዓ ምንነት በሚከተለው መልኩ አጠናቅረናልና ተከተሉን ። የኋላ ታሪክ ዛሬ የምናነሣት የዐብደላህ አልሀረሪ (አልሀበሺ) ጀመዓ የቅርብ ጊዜ ታሪክ ነው ያላት ። በምድር ላይ የሃምሣ አመት እድሜ እንኳን አልሞላትም ። የተመረሠተችው በሊባኖስ ሲሆን መሥራቹም የኛው ሰው ናቸው ። ሙሉ ሥማቸው ዐብደላህ ኢብኑ ሙሀመድ አልሀረሪ (አልሀበሺ) ይባላል ። በሀረር ከተማ ከአደሬ ብሄረሰብ ነው የተወለዱት ። አልሀበሺ የዘር ሀረጋቸው ከቁረይሽ ጎሣዎች አንዷ ከሆነችው ከበኒ ሸይባህ እንደሚመዘዝ ይነገራል ። ተከታዮቻቸው እሣቸው ይዘው የመጡትን ዐቂዳ / እምነት / ታላቅነት ለማመልከት የዘራቸውን ታላቅነት ይጠቅሣሉ ። በሌላ በኩል ግን ይህንን ጉዳይ የማይጋሩ በርካቶች ናቸው ። ናቸው ቢባል እንኳ ከተከበረ ዘር መሆንንና መልካምነትን የሚያገናኛቸው ነገር አለመኖሩን በርካታ ምሣሌዎችን በመጥቀስ ማስረዳት ይቻላል ። የዚህ ኡመት ፈርዖውን በመባል የሚታወቀውና በነቢያችን ሰለላሁ ዐለይህ ወሠለም ዘመን ዋና የኢስላም ጠላት የነበረው አቡጀህል ከቁረይሽ ጎሣ መሆኑን ልብ ይሏል ። በቁርኣን ከባድ እርግማን የወረደበት አቡለሀብም ቢሆን የነቢያችን ሰላላሁ ዐለይህ ወሠለም አጎት የነበረ ስለመሆኑ አንዘንጋ ። ዐብደላህ አልሀበሺ በልጅነታቸው በሀረር ገጠራማ አካባቢዎች የዐረብኛ ቋንቋና የሻፊዒይን ፍቅሂ ተምረዋል ። ሌሎች ሃይማኖታዊ ትምህርቶችንም ከተለያዩ መሻኢኮች ቀስመዋል ። የማይጨበጠው አቋማቸው ዐብደላህ አልሀበሺ ከወጣትነት እስከ ሽምግልና በዘለቀው የህይወት ዘመናቸው አንድ አይነት አቋም ይዘው ሲጓዙ አልተስተዋሉም ። ለበርካታ ጊዜያት በሱፊያ አመለካከቶችና መንገዶች ውስጥ ሲወጡና ሲገቡ ቆይተዋል ። ሀረር እያሉ ቃዲሪያ የሚባል ጠሪቃ መንገድ ተከታይ ነበሩ ። ወደ ጅማ ሲሄዱ ደግሞ ቅልጥ ያሉ ቲጃኒ እንደነበሩ ይነገራል ። ከዚህም በተጨማሪ በየጊዜው የሚፈፅሟቸው ድርጊቶች ለብዙዎች ግራ የሚያጋቡ ነበሩ ። ሼክ አህመድ አድደውለዊ ስለሣቸው ያዩትን ሲናገሩ ‘ይህ ሰው በአንድ ወቅት ጅማ ሄዶ ሲመለስ በቲጃኒ ጠሪቃ ላይ ተመስርቶ አላህን የሚያወሣበት መስገጃው ላይ ተቀምጦ በዙሪያው ስድስት ሲጃዳዎች አንጥፎ አየሁት ። ስለዚህ ሁኔታ ተጠይቆም አንደኛዋ ሲጃዳ ለነቢዩ ናት ፤ ሁለተኛዋ ደግሞ ለኢማም አህመድ አትቲጃኒ ስትሆን የቀሩት አራቱ ደግሞ አውራዱ (አላህን ማውሣቱ) ላይ ይገኛሉ ተብለው ለሚጠበቁት ለአራቱ ኸሊፋዎች እንደሆኑ ተናግሯል ። አልሀበሺ ሀረር ተመልሰው ጥቂት እንደቆዩ ግን ይህን ጠሪቃ ተው ። ቲጃኒዎችንም ማክፈር ጀመሩ ። ወደ ሊባኖስ ሲሻገሩ ደግሞ የሪፋዒ ጠሪቃ ተከታይ እንደሆኑና ከሌሎች የሚሻለውም ይሀው መንገድ እንደሆነ ያስተምሩ ነበር ። በሊባኖስ ቆይታቸው ጥመትና አልባሌ ነገሮች ከሞላባቸው ከተለያዩ የፍልስፍና መንገዶች የተለያዩ አመለካከቶች መቅዳትና መገልበጥ ያዙ ። ውርሣቸውም ይህን ይመስላል – በኢማን / እምነት/ ጉዳይ ላይ ከኸዋርጆች (አፈንጋጮች) ጋር በማበር ሙስሊሞችን ማክፈር ጀመሩ ። ጀህሚያ እና ሙዕተዚላ ከሚባሉ ጀመዓዎች ደግሞ ደግሞ የአላህን መልካም ሥሞችና ባህሪዎች በመቁረጥ አሊያም በመቀጠል ለቁርኣን አንቀፆች ያልሆነ ትርጉም መስጠትን ወረሡ ። ከሺኣዎች ደግሞ እነ ሙዓዊያን እና ዐምር ኢብኑልዓስን ጨምሮ ታላላቅ ሰሃቦችን የመስደብ ትልቅ ወንጀል ተጋሩ ። ከአህለልኪታቦች ደግሞ በተወሱል ሰበብ መቃብር ለመቃብር አማላጅ ፍለጋ መንከራተትን በትምህርታቸው ውስጥ አካተቱ ። ሸኹ እንዲህ የተሠባጠረ አካሄድ የሚከተሉ ከመሆናቸው የተነሣ የሣቸው መንገድ ይህ ነው ብሎ በግልፅ ለማስቀመጥ ይቸግራል ። አመለካከታቸው ሸኽ ዐብደላህ አልሀበሺ ከትንሽነታቸው ጀምሮ በባህሪያቸው አስቸጋሪ ሰው እንደነበሩ ይነገርላቸዋል ። ትክክል ነኝ ብለው ባመኑበት ነገር ከሸኾቻቸውና አስተማሪዎቻቸው ጋር ክርክር በመውደድ ይታወቃሉ ። በዚህም የተነሣ በየጊዜው ከሚያስተምሩዋቸው ሸኾች ጋር ውዝግብ ውስጥ ይገቡ ነበር ። ሰላትን ማንንም ተከትሎ ለመስገድ ፈቃደኛ አይደሉም ። ከሰዎች ጋር ላለመስገድ ሲልም ሰላታቸውን ያዘገዩ ነበር ። ከዚህም በላይ ሰዎች በሰላትና በቂርኣት በጥንቃቄ እንዲጨናነቁ ያስገድዳሉ ። የገዛ ሸኻቸውን ጭምር ተከትለው የማይሰግዱ ሲሆን ክስተቱም አንድን ሙስሊም ለማነወርና ለማክፈር ዳርዳርታውን የጀመሩበት ወቅት ነበር ። ላለመስገድ እንደምክኒያትነት ያቀርቡ የነበረውም ኢማማቸው በዐረቢኛ የፊደል አወጣጥ (መኻሪጀልሁሩፍ ) ላይ ችግር አለባቸው የሚል ነበር ። በወቅቱ ከተማሪያቸው ይህን ያስተዋሉት ሸህም ‘ ይህ ሰው ወደፊት የፊትና ሰው ( ሰዎች በሱ የተነሣ የሚወዛገቡበት ) ነው የሚሆነው ።’ እስከማለት ደርሰዋል ። ዘግይቶም ቢሆን የሸኹ ትንበያ የሠመረ ይመስላል ። ዛሬ ዓለማችን እሣቸው ባመጡትና ከአራቱም መዝሀብ ውጭ በሆነው አዲስ አመለካከት ችግር ውስጥ የገባች ስትሆን በዋናነት ደግሞ ያደጉባት ሀገር ሊባኖስ ትልቅ ፈተና ውስጥ ናት ። ሸሁ የዛሬ ሁለት አመት አካባቢ ይህችን ዓለም በሞት ቢሰናበቱም የለኮሱት ፊትና ግን ዛሬም ከሀገር ሀገር እየዘለለ ነው ። ሸኹና ተከታዮቻቸው ብዙ ክርስቲያኖች ሺዓዎችና የተለያዩ አልባሌ እምነት ተከታዮች በሚገኙባት በዚህች ሀገር እግራቸውን ሊያቆሙ የቻሉት ለሱና ሰዎች ባላቸው ጥላቻ የተነሣ ከምእራባውያን ፣ ከሺዓዎችም ሆነ ከሌሎች የኢስላም ጠላቶች ከፍተኛ ድጋፍ ስለሚደረግላቸው ነው ይባላል ። ማክፈር … ትልቁ መፈክር ዐብደላህ አልሀበሺ ለማንኛውም ‘ ይቃወመኛል አሊያም አመለካከቴን አይጋራም ’ ብለው ባመኑት ሰው ላይ ረጅም ምላሣቸውን ለመልቀቅ ወደኋላ አይሉም ። እሣቸውም ሆኑ ተከታዮቻቸው አንድን ሰው ለማክፈር እጅግ ሲበዛ ችኩሎች ናቸው ። በተለያዩ የሀገራችን ክፍሎች የሚገኙ ሱፊዮች እስከዛሬ ድረስ ሰውን ሲያከፍሩ አልተስተዋለም ። አሁን የአህባሽ አመለካከት ከመጣ ወዲህ ግን እነሱም ወደማክፈር ገብተዋል ። ዐብደላህ አልሀበሺ ‘ አትተዓዉን ዐላ ነህይ ወልሙንከር ’ ( በመጥፎ ነገር ላይ መረዳዳት ) በሚለው ኪታባቸው ላይ እንደፃፉትም ከትላልቅ ዓሊሞች ውስጥ የሚያስቀሩት ጥቂቶችን ብቻ ነው ። ኪታባቸው ከመጀመሪያ እስከመጨረሻ ተህዚር ! ተህዚር… ! ተጠንቀቁ ተጠንቀቁ .. ! በሚል ማስፈራሪያ የተሞላ ነው ። ካለፉትም ይሁን በህይወት ካሉት ዑለማኦች ፣ ዳዒዎችና የኢስላም ተንታኞች ውስጥ ሰዎች ሊሸሿቸው የሚገባቸውን አንድ በአንድ ይዘረዝራሉ ። ዓሊሞቹ የተናገሯቸውን ቃላት በመምዘዝም ‘ እገሌ በአንድ ወቅት እንዲህ ብሏል እገሌም እንዲህ ብሏል … እያሉ እራሣቸውን የዚህች ዓለም ብቸኛ ነቢይ አድርገው የማስቀመጥ ያህል ይፈርዳሉ ። ሲሻው ይሣደባሉ ፤ ካልሆነም ይራገማሉ ፤ ባስ ካለም ያከፍራሉ ። ስድባቸውን የሚጀምሩት ከታላቁ ሰሃባ ከሙዓዊያ ኢብኑ አቢሱፍያን ነው ። ስለ ዐምር ኢብኑል ዓስና ስለ እናታችን ዓዒሻም የሚሉት አላቸው ። ይህም ያለ አንዳች ኤዲቲንግ (ማስተካከያ) ከሺዓዎች የገለበጡት ቀጥተኛ የሆነ አቋማቸው እንደሆነ ብዙዎች ይስማሙበታል ። ከሰለፍ ዑለማኦች እነ ዳርሚይንና ኢብኑ ኹዘይማህን ወርፈዋቸዋል ። የተውሂድ አቀንቃኙ ኢብኑ ተይሚያህ ዋና ጠላታቸው ሲሆኑ ‘ ካፍር (ከሀዲ) ፤ ሙርተድ (ከኢስላም ወደ ክህደት የተመለሠ )’ በማለት ይገልጿቸዋል ። በተገኙበት ሁሉ ኪታቦቻቸው እንዲቃጠሉ አዘዋል ። የኢብኑ ተይሚያን ተማሪ ኢማም ኢብኑ አልቀይም አልጀውዚን እና ታላቁን ሙፈሲር (የቁርኣን ተንታኝ) ኢብኑ ከሲርንም አክፍረዋል ። ኢማም ዘሀቢን ኸቢስ (መጥፎ) ሲል ይዘልፏቸዋል ። ታላቁ የሀዲስ ሰው ሸይኸ አል አልባኒ ፣ የሳዑዲ ሙፍቲ የነበሩት ሸኽ ኢብኑ ባዝና ታላቁ ዓሊም ኢብኑ ዑሰይሚን እንዲሁም የወቅቱ የዓለም ሙስሊም ዑለማኦች ዋና ፀሃፊ የሆኑት ሸኽ ዶ/ር ዩሱፍ አል ቀርዳዊም በካፍርነት ከተፈረጁ መካከል ናቸው ። ሰዎች እንዲጠነቀቋቸው ከፃፉባቸው ሌሎች ሰዎች መካከል ታዋቂው ዳዒ ዶክተር ዐምር ካሊድ ፣ ፈይሰል መውለዊ ፣ ፈትሂ የኩን የመሣሠሉት ሲገኙ ዓለም አቀፍ እውቅና ያላቸው ምሁራን ይገኙባቸዋል ። የሱፊያው መሪ ሸኽ ሙሀመድ ሰዒድ አልቡጢ ውግዘቱ ተርፎአቸዋል ። ዶክተር ዛኪር ናይክና የፒስ ቲቪ ባልደረቦቹም በክህደት ከተወነጀሉት ውስጥ ናቸው ። አልሀበሺ ታላቁን የፍቅሂ ሰው ሰይድ ሳቢቅን መጁሲ /እሣት አምላኪ/ ሲል ይገልጿቸዋል ። ሰይድ ቁጥብን ከመራገም አልፈው እሱንና ተከታዮቹን በስቅላት በመግደሉ ለጀማል አብዱናስር ታላቅ አድናቆት አላቸው ። የስደቱ ምክኒያት ‘ አልሀበሺ አክጣኡሁ ወሹዙዙሁ /አልሀበሺ ስህተቶቹና ድልጠቶቹ / ’ የምትለውና በዐብዱረህማን አድ ድመሽቂያህ የተዘጋጀችው ትንሽ መፅሃፍ አንደምታትተው ከሆነ አልሀበሺ ከትውልድ ሀገራቸው ኢትዮጰያ ሸሽተው የወጡት በሀረር ሙስሊሞች መካከል ውዝግብ በማስነሣታቸው ነበር ። በወቅቱ የሀረር ገዠ ከነበሩት የሃይለሥላሴ አማች አንዳርጌ ጋር በመተባበር በሀረር የሚገኙ የቁርኣን ሂፍዝ ማዕከላትን ማስዘጋታቸውም ተነግሯል ። ጊዜውም በ1940 ዓ.ል ነበር ። በወቅቱ ወደ ተውሂድ ጥሪ የሚያደርጉ ዑለማኦች በአልሀበሺ ውንጀላ ከፍተኛ መንገላታታ የደረሠባቸው ሲሆን በርካቶች ወደ ግብፅና ሳዑዲ ዐረቢያ በመሰደድ ህይወታቸውን ሲያተርፉ የተቀሩት ደግሞ እንዲታሰሩና በጨቋኙ መንግስት እንዲዋረዱ ተደርጓል ። ሰዎችንም የሚያሣስሩበት ዋና ምክኒያትም ዛሬም ተከታዮቹ እንደሚወነጅሉት ‘ ወሃቢያ ነው ’ በማለት ነበር ። ሆኖም ግን ኋላ ላይ ተነቅቶባቸው እራሣቸው የለኮሱት እሣት ሊፈጃቸው እንደሆነ ሲረዱ የታሠሩና የተገደሉ ሰዎች ቤተሰቦችን በቀል በመፍራት ከሀጃጆች ጋር በመሆን በሶማሊያ በኩል አድርገው ሣዑዲ ሊገቡ ችለዋል ። ሸሁ ቀጥለውም ወደ ሀገረ ኢስራኤል ኋላም ወደ ሶሪያ በመሻገር በመጨረሻም ሊባኖስን ማረፊያቸው አደረጉ ። በሊባኖስ ቆይታቸውም ዓሊም መስለው በመቅረባቸው ብዙዎች በሣቸው ተታለዋል ። መጀመሪያ አካባቢ የተለያዩ አንዳንድ መፅሃፎችን በማረም ወደ ማህበረሰቡ ውስጥ ገቡ ። ቀጥሎም ለየት ያለ አዲስ አመለካከታቸውን ማስተዋወቅ ያዙ ። ተውሂድ ይዞ የነበረውን ህዝብም ወደኋላ አንሸራተቱ ፤ በፍቅር ይኖር በነበረው ማህበረሰብ መካከል ፍትናን በማሠራጨት ጥላቻን በመንዛታቸውም አንድነታቸው ተበተነ ። ሀይላቸውም ተዳከመ ። ቁጥራቸው ስንት ይሆን በዓለም ላይ የአህባሽ ተከታዮች ቁጥር ከ250 ሺህ እንደማይበልጥ ይገመታል ። የዓለም ሙስሊሞች ቁጥር ወደ ሁለት ቢሊዮን የተጠጋ ሲሆን በነሱ እይታ ከነሱ ውጭ የሆነው ሙስሊም ሁሉ ካፍር በአላህ ያላመነ ከሀዲ ነው ማለት ነው ። እስልምናቸውም ትክክል ስላልሆነ እንደገና ሸሃዳ እንድይዙ ይመክራሉ ። አህባሾች በእምነት ጉዳይ ከሺዓዎች የሚጋሯቸው በርካታ አመለካከት ያሏቸው ሲሆን ህዝቡላህን ከመሣሠሉ በኢራን ከሚደገፍ ፓርቲም ትልቅ ድጋፍ ያገኛሉ ። የሱና ጀመዓዎችን ለመቃረን ሲሉ ብቻ ከጥመትና ከኩራፋት ጀመዓዎች ጋር ፍቅራቸው እጅግ የጠነከረ ነው ። መሪዎቻቸውም ሆኑ ተከታዮቻቸው በስሜት የሚነዱ ፣ ለጥቅም ያደሩ ፣ ሥነምግባርና ዘመናዊ እውቀት የጎደላቸው ናቸው ። የሚያንቀሳቅሷቸው ድብቅ የሆኑ የሙስሊሙ ጠላት እጆች እንዳሉባቸው የብዙዎች ግምት ነው ። ሱፍያ ፣ አል አሽዐሪይ ፣ ኢማሙ ሻፊዒይና አህባሽ አህባሾች ‘ ሱፊዮች ነን የኢማም አሽ ሻፍዒና የአሽዓሪይ መዝሀብ ተከታዮች ነን ቢሉም አመለካከታቸው በብዙ መልኩ ከነሱ የተለዩ ነው ። ሱፊዮች ሙስሊሙን ሲያከፍሩ በታሪክ አልታየም ። ‘ ቁርኣን የአላህ ንግግር አይደለም ’ አይሉም ። ከመካና መዲና ኢማሞች ኋላ እንዳይሰገድም ብይን አያስተላልፉም ። ከካፍሮች (ከሀዲያን ) ጋር አብረውም ሙስሊሙን አይበድሉም ። ከነቢዩ ሰለላሁ ዐለይህ ወሠለም ሰሃቦች አንዱን እንኳ አይሰድቡም ። እነሱ ‘ እንከተላቸዋለን ’ የሚሏቸው ኢማሙ ሻፊዒይም ከአካሄዳቸው ፍፁም የጠሩ ናቸው ። ኢማሙ በቀደምት ሰሃቦች መካከል ስለተፈጠረው ልዩነት ደፍረውና አፋቸውና ሞልተው ለመናገር አላህን ይፈራሉ ፤ ኢማሙ ሻፊዒይ ‘ ያች በርግጥም ትልቅ ፈተና ናት ። አላህ ሱብሃነሁ ወተዓላ ከሷ እጃችንን አጥርቶልናል ። ታዲያ ምላሣችንን ማጥራት አይጠበቅብንም ’ ሲሉ በቀደምት ሰሃቦች ውስጥ የተከሰተውን ነገር ከመተንተን ይቆጠባሉ ። ኢማሙ ሻፊዒይ ሪባን /ወለድን / ም ሆነ ሰው ማጭበርበርን አይፈቅዱም ፣ ዘካን ከእስልምና አላስወጡም ፣ ለአላህ ባህሪያት ያለትርጉማቸው ትርጉም አልሠጡም ። ዋና ዋና አመለካከት v ቁርኣን የመልአኩ ጅብሪል እንጂ የአላህ ንግግር አይደለም ይላሉ ። ቁርኣን የአላህ ንግግር ስለመሆኑ የሙስሊሞች ሁሉ እምነት ነው ። v በነሱ ጥላ ሥር ያልተጠለለውን ማንኛውንም ሙስሊም ሁሉ ካፊር ነው ይላሉ ። እውነተኛ ሙስሊም ማለት የነሱን አካሄድ የተከተለ አመለካከታቸውን የተጋራ ነው ። ከሀዲ ማለትም ከነሱ መንገድ የወጣ ነው ። አመለካከታቸውን ያልተቀበለውን ሙስሊም ስለሚያከፍሩ ተከትለውት አይሰግዱም ። ማክፈር በነሱ ዘንድ እጅግ ቀላል ነገር ነው ። አንድ ካፊር ያልሆነውን ሙስሊም ወንድሙን ካፊር ያለ ሰው ንግግሩ ወደሱ ተመላሽ እንደምትሆን ነበያችን አስተምረውናል ። v ‘ የሀረም ( የመካና መዲና ) ኢማሞችን ተከትሎ መስገድ ሀራም ነው’ ይላሉ ። ለሀጅ የሚሄድ ሰው እነሱን ተከትሎ መስገድ የለበትም ቢሰግድም ሰላቱ ትክክል አይደለም ብለው ያምናሉ ። ኢማማቸው አልሀበሺ ይህንን ያደረጉ እንደሆነ ደግመው እንዲሰግዱ ያዛቸዋል ። ለምን ቢባል በነሱ አመለካከት የሀረም ኢማሞች ከሀዲዎች ናቸውና ነው ። በዚህ አይነት በርካቶችን የሀረም ተስግዶ የሚገኘውን ከፍተኛ አጅር አሣጥተዋል ። v የአላህን መልካም ባህሪያትና ሥሞች መካዳቸው ሌላው ነው ። አላህ ስለራሱ የተናገራቸውን ነገሮች ትርጉሙን በማጣመም ይተረጉማሉ ። ሲሻቸው ይቀንሣሉ ባሰኛቸውም ጊዜ ይጨምራሉ ። ቀደምት ሰለፎችና በተዋረድ እነሱን የሚከተሉ ሙስሊሞች ግን አላህ ሱብሃነሁ ወተዓላ ስለራሱ በተናገረው መልኩ ያምናሉ ። እርሱ ለራሱ ያፀናውንም ባህሪ በሚገባው መልኩ ያፀናሉ ። v ሀጃቸውን ለማስፈፀም መቃብር አካባቢ ይመላለሣሉ ። ሙታኖች ሰዎችን ይረዳሉ ፣ ያግዛሉ ፣ ከጭንቅም ያላቅቃሉ የሚል እምነት አላቸው ። ከዚህም የተነሣ የአላህን በር ችላ በማለት ውሎአቸውን ደሪህ ካባቢ ያደርጋሉ ። የአላህ ወሊዮች ከመቃብር ወጥተው የሰውን ጉዳይ ፈፅመው የመመለስ ብቃት አላቸው የሚል እምነት አላቸው ። ከአላህ ሱብሃነሁ ወተዓላ ሥምም በላይ የወሊዮቹ ሥም ሲጠራ ይበረግጋሉ ። v በዲን ውስጥ አዲስ ፈጠራን /ቢድዓን/ ያበረታታሉ ። ‘ መልካም ነገር እስከሆነ ድረስ ቢጨመርበት ግድ የለውም ’ በማለት ከሃይማኖት አስተምህሮ ውጭ የሆኑ ነገሮችን ይጨማምራሉ ። በዚህም የተነሣ አምልኮአዊ ተግባራቶቻቸው ከነቢዩ ሱናዎች ይልቅ በሌሎች መጤ ፈጠራዎች የተጥለቀለቁ ናቸው ። v ኢማን ማለት የውስጥ እምነት ነው በሥራ ባይገለፅም ችግር የለውም የሚል አቋም አላቸው ። በመሆኑም በሸሪዓ ህግጋት ለመሥራት የተሠላቹ ናቸው ። ለሀላል ሀራሙም ነገር ግድ የላቸውም ። ይህም በመሆኑ በምድር ላይ የአላህ ህግ ተግባራዊ እንዳይሆን የሚፈልጉ በእጅጉ ይደግፏቸዋል ። ትክክለኞቹ ሙስሊሞች ግን ኢማን ማለት በቀልብ ውስጥ የሰረፀና በተግባርም የሚረጋገጥ ጉዳይ እንደሆነ ያምናሉ ። v ከአራተኛው ኸሊፋ ዐሊ ኢብኑ አቢጣሊብ ጋር በሀሣብ የተለያዩትን ሰሃቦችን እነ ሙዓዊያን እና ዐምር ኢብን አልዓስን ‘ ከአላህ ተእዛዝ የወጡ ናቸው ’ በማለት ይወርፏቸዋል ። ይህም የሺዓን አመለካከት የሚጋሩ መሆናቸውን አመላካች ነው ። በሊባኖስም ከሺዓዎች ጋር በመተባበር የሱና ጀመዓዎችን ሲያሣድዱ ይስተዋላል ። v አልሀበሺና ተከታዮቻቸው ከአመለካከታቸው ውጭ የሆኑትን ሙስሊሞች በመጥላት በመመቅኘትና እንዲሁም ሰሃቦች በመዳፈርና በመሣደብ ይታወቃሉ ። ይህም በመሆኑ በሊባኖስ ውስጥ ተስማምቶ ለመኖር የማያመች ወጣ ያለ የቁጣ ባህሪ ያለው ሰው ካጋጠመ የአል ሀበሺ ተከታይ እንደሆነ ይገመታል ። በሀገራችንም ውስጥ የምናየውም ሥራቸው ሰዎች ያላሉትን አሉ በማለት ትናንሹን ጉዳይ በማካበድ አንዳቸውን በሌሎች ላይ በማነሣሣት ነው ። ከአስገራሚ ፈትዋዎቻቸው በነጃሣ መስገድ ችግር የለውም ። ወለድ መብላት ይበቃል ። ሙስሊም ካልሆነ /ካፍር/ ጋር ቁማር ተጫውቶ መብላቱ ችግር የለም ። ችግር እስካልተፈራ ድረስ ። ሴትን ልጅ በተደጋጋሚ ማየቱ ነው እንጂ የሚከለከለው በመጀመሪያ እይታ ለረጅም ጊዜ ማየቱ ይበቃል ። ሴት ልጅ በየትኛውም ጊዜ ያለባሏ ፈቃድ ሽቶ ተቀብታና ተኳኩላ መውጣት ትችላለች ። ኢክቲላጥ /የሴቶችና ወንዶች ቅልቅል/ ችግር የለውም ። ለዚህም ሲባል ተከታዮቻቸው የሆኑ ወንድና ሴቶች ተቀላቅለው ይጨፍራሉ ። ሙስሊም ወዳልሆኑ ሀገሮች የሚሄድ ሰው ችግር ይገጥመኛል ብሎ የሚፈራ ከሆነ መስቀል ማንጠልጠል ይችላል ። ዘካ በወርቅና ብር እንጂ በወረቀት ገንዘብ ግዴታ አይሆንም ። ሆን ብሎ መዘግየትና መስነፍ ችግር የለውም ። ለምሣሌ ጁሙዓና ጀመዓ ላለመምጣት የፈለገ ሰው ነጭ ሽንኩርት መብላት ይችላል ። መኻሪጀልሁሩፍ /የዐረብኛ ቃላትን በትክክል ማንበብ ማይችሉ/ አሰጋጆችን ተከትሎ መስገድ አይበቃም ። ለሴት ልጅ ከላይ ሂጃብ እስከለበሠች ድረስ ከታች ጠባብ ጂንስ ብትለብስም ችግር የለውም ። በአንድ ወቅት በአህባሽ ብይን የተነሣ በአሜሪካና ካናዳ የሚገኙ ሙስሊሞች ከከዕባ አቅጣጫ 90 ድግሪ ያህል ዞረው ሰግደው ነበር ። ይህ ነው እንግዲህ ከእስልምና አስተምህሮ ወጣ ያለው ጥፋታቸውና አስቀያሚ አካሄዳቸው ። ልብ ያለው ልብ ይበል ። አደገኝነታቸው የአህባሽ አመለካከት ወደ አንድ ሀገር አይደርስም የሚከተሉት ነጥቦች ቢከተሉት እንጂ የሰዎች ለሰዎች ማህበራዊ ግንኙነት ይበላሻል ፣ የሙስሊሙ አንድነት አደጋ ውስጥ ይገባል ፣ ሽኩቻ ጥላቻና ውጥረት በመካከላቸው ይነግሣል ። ሙስሊሞች መሣቂያ መሣለቂያ ይሆናሉ ። በምእመናን መካከል መተሣብና መተዛዘን ይጠፋል ፣ አሉባልታና የውሸት ወሬ ይስፋፋል ። ከሱና ይልቅ ቢድዓ ቦታ ያገኛል ፣ ከቁርንና ሀዲስ በበለጠ መሠረተ ቢስ ታሪኮችና ትረካዎች /ቂሳዎች/ ይገናሉ ፣ ከታላቁ ነቢይ ሥም በላይ የወሊዮችና የሸሆች ሥሞች ይዘወተራሉ ። የአላህ የአንድነት ትምህርት ይሸረሸራል ሽርክና ወደ ሽርክ የሚያደርሱ መንገዶች ክፍት ይሆናሉ ፤ ተውሂድ በሽርክ ይተካል ፣ ንቃት በመሃይምነት ይተካል ፣ ብስለት በስሜታዊነት ፣ እዝነት በጭካኔ ፣ መተማመን በጥርጣሬ ፣ መቻቻል በብጥብጥ ይተካል ፣ ሚዛናዊነት በአክራሪነት ፣ አርቆ አስተዋይነት በችኩልነት ይተካል ። ከዚህም ባለፈ ሂጃብ በሱሪ ይተካል ፣ ቁርኣን በተለያዩ ሀድራዎችና ሙዚቃዎች ይተካል ። መናፍቃን ቦታ ያገኛሉ ፣ የሱና ሰዎች ይጠላሉ ፣ በኢስላም ሀግጋት ለመሥራት ደፋ ቀና የሚሉ ‘ አክራሪ ፣ አሸባሪ ’ ይባላሉ። አለማቀፍ ዓሊሞች ምን ይላሉ ከተለያዩ ሀገራት የተውጣጡ ከሱፊያም ሆነ ከሌላ ጀመዓ የሆኑ የአራቱ መዝሀብ አለማቀፍ እውቅና ያላቸው የዘመናችን ዓሊሞች ከዚህ ጀመዓ በማስጠንቀቅ ረገድ አንድ ሆነዋል ። v አብዛኛዉ ዓሊሞቹ በሱፊያ መዝሀብ ላይ የሚገኙት የግብፁ ታላቁ ኢስላማዊ ተቋም አል አዝሀር እነሱን አላውቃቸውም ብሏል ። ጠማሞች ስለመሆናቸውም በተደጋጋሚ ገልጿል ። የአዝሀር ዩኒቨርስቲ ዳይሬክተር አህመድ ዑመር ሃሽም ‘ ይህ ጀመዓ በቁርኣንም ሆነ በሀዲስ የማይመራ ነው’ ብለውታል ። v የሊባኖሱ ሙፍቲ ሸኽ ኻሊድ ሀሠን ከሀገሪቱ መንግስት ርእሰ ብሄር ረሺድ ከራሚ በአንድ ወቅት ዐብደላህ አልሀረሪ ከሀገር ወጥቶ በነበረበት ወቅት በሱና ሰዎች ላይ በሚያደርገው አደገኛ አካሄድ የተነሣ ወደ ሀገር ወስጥ እንዲገባ እንዳይፈቀድለት ጠይቀው የነበረ ሲሆን ለጥቂት ጊዜ ታግዶ ነገር ግን በተለያዩ ምእራባውያን ሀገራት ግፊት የተነሣ ሊገባ ችሏል ። v የግብፁ ሙፍቲ ዶክተር ዐሊ ጁሙዓ ‘ ሥሙ ዐብዱላህ አልሀረሪ አልሀበሺ የሚባል ሰውየመሠረታት ይህች ጀመዓ ውስጣዊና ውጫዊ ገፅታም አላት ። ውጫዊ ገፅታዋን ስናይ በፍቅሂ የሻፊዒይ መዝሀብ ተከታይ ፣ በዐቂዳ ደግሞ አሽዐሪን ይመስላሉ ። ውስጣዊ ተልእኮዋ ግን ያላግባብ ሙስሊሞችን ማክፈር፣ ምእመናን ያላግባብ መወንጀልና በሀዝቦች መካከልል ውጥረትና ውዠንብር መፍጠር ነው ። ለዱኒያዊ ጥቅም ሲሉም ለኢስላም ጠላቶች ይሠራሉ ። ብለዋል ። v በአውሮፓ የሙስሊም ኮሙኒቲ ሙፍቲ የሆኑት ዶክተር ፈይሰል መውለዊ ‘ የዐብደላህ አልሀረሪ ተከታዮች የሆኑት አህባሾች በጥቃቅን ነገሮች ሙስሊሙን ዑለማ የሚያከፍሩ ፤ አብዛኞቹ የሰለፍ ዑለማኦች የማይጋሯቸው የሆኑ የራሣቸው የሆነ አመለካከት /ዐቂዳ / ያላቸው ቡድኖች ናቸው ። ከሸኻቸው ውጭ ስለማይቀበሉ ከነሱ ጋር መነጋገር ጥቅም የለውም ። ከነሱ ጋር ላለመከራከር መስጅዳቸውን መሸሽ ይገባል ። ። እነሱ ከነሱ ውጭ የሆነውን ‘ ከሀዲ ነው ከነሱ በኋላ መስገድ አይበቃም ’ ብለው ቢያምኑም እኛ ግን ሙስሊሞች እንደሆኑና ከነሱ ጋርም ሆነ ተከትለዋቸው መስገዱ ይበቃል የሚል እምነት አለን ። v የዓለም ሙስሊም ዑላማኦች ፕሬዚዳንት የሆኑት ዶክተር ሼከ ዩሱፍ አልቀረዷዊም ‘ እነሱ የሚወክሉት የተወሰነ የማህበረሰብ ክፍል ብቻ ነው ። የሙስሊሙን የጋራ አቋም /ኢጅማዕ/ በመጣል ተለይተው የወጡ ናቸው ። የሙስሊም ዑላማኦችን አክፍረዋል ። አህባሾች በጥመት ውስጥም በጣም የሰጠሙ ናቸው ። ኢማም ዘሀቢን ፣ ኢብኑ ተይሚያን ፣ ኢብኑልቀይምን ፣ ኢማም ገዛሊን ፣ ኢብኑ ዐብዱልወሃብን ፣ ኢብኑ ባዝን ፣ ሰይድ ቁጥብን አንዱንም ሣይተው አክፍረዋል ። መሃይማን ብቻ ሣይሆኑ ድርብ ድርብርብ መሃይሞች ናቸው ። ሁኔታቸው አላህ እንዳለው ነው “ ሰዎች እንዳመኑት እመኑ በተባሉ ጊዜ ሞኞች እንዳመኑት እናምናለን እንዴ! ” ይላሉ ። v የሶሪያው የሱፊያ ዓሊም የሆኑት ዶክተር ሙሀመድ ሰዒድ አልቡጢም ‘በበይሩት ዐብደላህ አልሀረሪ የሚባል ኢማም ያላቸው አህባሾች ወሃቢያን ተከትሎ መስገድ አይበቃም ፣ ኢብኑ ተይሚያ ካፊር ነው ይላሉ ። በመሠረቱ ወሃቢን ተከትሎ መስገድ ሀራም አይደለም ። ተከትሎ የሰገደም ሰላቱ ትክክል ናት ። አንድን ሙስሊም ማክፈር ይበቃም ሲሞት በኩፍር ላይ ሆኖ ስለመሞቱ ማረጋገጫ እስካልተገኘ ድረስ ። ስለሷ የምታነሱልኝ ጀመዓ ብዙ ሙስሊሞችን ያከፍራሉ ። ሙተወሊ ሸዕራዊን ቀርዷዊን እኔንም ያከፍራሉ ። ምናልባት ሙስሊሞች እነሱ ብቻ ሣይሆኑ አይቀሩም ።’ ብለዋል ። v በሊባኖስ የሙስሊም ጀመዓዎች ተጠሪ የሆኑት ፈትሂ የኩን ‘ ዐብደላህ አልሀረሪም ሆነ ድርጅቶቹ ቀደምት ሰለፎችና የዚህ ኡመት ሚዛናዊ አመለካከት ያላቸው ምሁራን የጋራ አቋም የያዙበትን ነገር የሚቃረኑ ናቸው ።’ ብለዋል ። v በኢስላማዊ ብይኖች የበላይ የሆነው የሰኡዲ ቋሚ የሆነው የእውቀትና የፈትዋ ኮሚቴ በአንድ ወቅት ‘ ዐብደላህ አልሀረሪ ኢስላምን አገለገለ ወይንስ አወደመው ? ’ ተብሎ በተጠየቀ ጊዜ እንዲህ በማለት መልስ ሰጥተዋል ። ‘ በሥም ተጠቃሹ እጅግ መጥፎ ሰው ነው ። በዘመኑ ካሉ የቢድዓና የጥመት መሪዎችም አንዱ ነው ። እሱም ሆነ ተከታዮቹ ሆንብሎ ነቢያችን ሰለላሁ ዐለይህ ወሠለም ሰሃቦችና ታቢዒዮች ያስተላለፉልን የሙስሊሞችን ቀደምት አመለካከት /ዐቂዳ / ለማጥፋት ቆርጦ የተነሣ ሰው ነው ። በፍቅሂ ዙሪያ የራሣቸው የሆነ አካሄድ አዘጋጅተዋል ከቁርኣንም ሆነ ከሱና ሰንሰለት በሌላቸው ለየት ባሉ እና በዘቀጡ አመለካከቶች የተሞሉ ናቸው ። በዐቂዳና በሥራ በኩል ከፍተኛ የሆነ ችግር አለባቸው ። የዚህን ኡማ ታላላቅ መሪዎች በማነወርም ይታወቃሉ ። ሁሉንም ሙስሊሞች ከነኚህ ጠማማ እና የተንሸራተተ ጀመዓ እንዲሁም ወጣ ካለ አመለካከታቸው እንዲጠነቀቁ እንመክራለን ።’ ብለዋል ። v ታላቁ የሀዲስ ሰው ሼኽ ሙሀመድ ናስረዲን አል አልባኒም ‘ አህባሾች የዐብደላህ አልሀረሪ ተከታዮች ናቸው ። አመለካከታቸው በአጉል ፍልስፍና ላይ የተመሠረተ ሲሆን ቁርኣንና ሀዲስን በዐቅላቸው በመመራመር እንጂ በሰለፎች ግንዛቤ ላይ አይረዱም ። ተጠቃሽ ምንጮች ﺑﻐﻴﺔ ﺍﻟﻄﺎﻟﺐ ﻟﻠﺸﺒﺦ ﻋﺒﺪ ﺍﻟﻠﻪ ﺍﻟﻬﺮﺭﻱ ﺍﻟﺤﺒﺸﻲ ﺃﺧﻄﺎﺀﻩ ﻭﺷﺬﻭﺫﻩ ﻋﺒﺪ ﺍﻟﺮﺣﻤﻦ ﺍﻟﺪﻣﺸﻘﻴﻪ ﺻﺮﺑﺢ ﺍﻟﺒﻴﺎﻥ ﻟﻠﺸﺒﺦ ﻋﺒﺪ ﺍﻟﻠﻪ ﺍﻟﻬﺮﺭﻱ ﻓﺮﻗﺔ ﺍﻷﺣﺒﺎﺵ ﺩ ﻋﻠﻲ ﺍﻟﺸﻬﺮﺍﻧﻲ Antihabashis.com, alsunnah. org qaradawi.net Bouti.com

መዋቅር[ኮድ አርም]

መጣጥፉ መዋቅር ከሆነ የጠቅላላ ወይም የተወሰነ የመዋቅር መለጠፊያ ከግርጌ መለጠፊያዎች (ካሉ) ስር ይጨምሩ።

መደቦችና የሌሎች ቋንቋዎች መያያዣዎች[ኮድ አርም]

መደቦች ከመዋቅር መለጠፊያዎች (ካሉ) በታች ይቀመጡ። ተዛማጅ የሌሎች ቋንቋዎች መያያዣዎች ምርጥ ጽሁፍ (Featured article / Good article) ከሆኑ ከመደቦች በታች ያመልክቱ።