ቅዱስ ገብረክርስቶስ

ከውክፔዲያ
ቅዱስ ገብረክርስቶስ
ሙሽራው ገብረ ክርስቶስ
ቅዱስ ገብረክርስቶስ ሞቶ ሲገኝ በእጁ ላይ ተጠቅልሎ የተገኘውን የሕይወት ታሪኩ ለአባቱ ለንጉሥ ቴዎድሲዮስ በእግዚአብሔር ትዛዝ በጳጳሱ ቴዎፍሎስ ሲነበበ የሚያሳይ ስዕል
ቅዱስ ገብረክርስቶስ ሞቶ ሲገኝ በእጁ ላይ ተጠቅልሎ የተገኘውን የሕይወት ታሪኩ ለአባቱ ለንጉሥ ቴዎድሲዮስ በእግዚአብሔር ትዛዝ በጳጳሱ ቴዎፍሎስ ሲነበበ የሚያሳይ ስዕል
ኢቺን ዓለም የናቀ የንጉሥ ልጅ
ስም አብድልመሲህ ሲተረጎም ገብረክርስቶስ
የአባት ስም ቴዎድሲዮስ
የእናት ስም መርኬዛ
ዜግነቱ ሮማዊ
የሚከበረው በክርስትና ሃይማኖት ተከታዮች
ያረፈበት ቀን ጥቅምት ፲፬
በዓለ ንግሥ ጥቅምት ፲፬ ና ግንቦት ፲፬ ከጫጉላ ቤት ወጥቶ የመኖከሰበት ቀን
የገብረክርስቶስን ስቃይ የሚያሳዩ ስዕሎች


ገብረክርስቶስ የቆንስታቲኖፕሉ ንጉስ ቲወዲሰይስ ልጅ የነበረ ጻድቅ ነው። የዚህ ጻዲቅና መባዓ ጽዮን የተባለው የኢትዮጵያ ጻዲቅ ገድሎች ተከለ ሃይማኖት በተባለ ሃብታምና ሚስቱ ወለተ ጽዮን አነሳሽነት ምክሖ ጊዮርጊስ በተባለ ፀሐፊ በአንድ መጽሃፍ እንዲጻፉ ተደረገ ።

ይህ መጽሐፍ እጅግ በተዋቡ ደማቅ ስዕሎች ያሸበረቀ ሲሆን ሰአሊው "ኢግናጦስ" የሚባል ሰው ሊሆን ይችላል በማለት ታሪክ ተመራማሪው ዋሊስ በጅ ገምቷል [1] መጽሃፉ በዓፄ ቴወድሮስ መቅደላ ላይ ሊያሠሩት ለነበረው ቤ/ክርስቲያናቸው እንደስጦታ አዘጋጅተውት በመሃሉ በእንግሊዞች ተወስዶ እንግሊዝ አገር ውስጥ ይገኛል ።

የመጀመሪ ሕይወት ታሪኩ[ለማስተካከል | ኮድ አርም]

ሙሽራው ገብረ ክርስቶስ

ሙሽራው ገብረ ክርስቶስ ወላጅ አባቱ የቍስጥንጥንያው ንጉሥ ቴዎዶስዮስና እናቱ ንግሥት መርኬዛ በስለት ያገኙት ብቸኛ ልጃቸው ስለሆነ ሃይማኖትን እያስተማሩት በምግባር በእጅጉ ተንከባክበው አሳድገውታል፡፡

የአባቱን ንግሥና በመውረስ ቍስጥንጥንያን እንዲገዛላቸው በመፈለግ ወላጆቹ ለአካለ መጠን ሲደርስ የሮሙን ንጉሥ ሴት ልጅ አጋቡት፡፡ እርሱ ግን ዓለምን ፍጹም በመናቅ የክርስቶስን መስቀል ለመሸከም የተዘጋጀ ነበርና የሠርጉ ዕለት ሌሊት የእርሱንም ሆነ የሙሽይቱን ድንግልና እንደጠበቀ ላንቺም ለእኔም ይህ ነገር የሚጠቅመን አይደለም[2] ብሎ ከጫጉላ ቤት ወጥቶ በመርከብ ተሳፍሮ ሩቅ ሀገር በመሄድ በቤተክርስቲያን ተቀምጦ ከነዳያን ጋር ተደባልቆ በመለመን ለምኖ ያገኘውንም ለሌሎች እየመጸወተ በጾም በጸሎት ተጠምዶ 15 ዓመት ኖረ፡፡

የዓላማው መታወቅ[ለማስተካከል | ኮድ አርም]

እመቤታችን ተገልጻ ለአንድ የቤተክርስቲያኑ አገልጋይ የገብረ ክርስቶስን ጽድቅ ብትነግረው ምሥጢሩን ለሀገሩ ሁሉ አዳረሰበት፡፡ ሙሽራው ገብረ ክርስቶስም ‹‹ግብሬ ታወቀ፣ ከዚህ ውዳሴ ከንቱ ልሽሽ›› በማለት ወደሌላ ሀገር በመርከብ ሲጓዝ ፈቃደ እግዚአብሔር መርከቢቱን ያለ አቅጣጫዋ ወስዶ አባቱ ደጅ አደረሰው፡፡ ማንነቱን እንደደበቀና ዓለምን ምን ያህል እንደናቃት ይረዳ ዘንድ በአባቱና በንጉሡ ደጅ የኔ ቢጤ ለማኝ ሆኖ ለአባቱ ውሾች የሚሰጠውን ፍርፋሪ እየተመገበ አሁንም 15 ዓመት ሙሉ በትዕግስት ተቀመጠ፡፡

የአባቱ አሽከሮች እንኳን እጣቢና ቆሻሻውን ሁሉ እየደፉበት ሲያሠቃዩት የአባቱ ውሾች ግን የእግሩን ቁስል ይልሱለት ነበር፡፡ በአጠቃላይ ገብረ ክርስቶስ እጅግ የተከበረ የታላቅ ንጉሥ ልጅ ሲሆን ነገር ግን ዓለምን ፍጹም በመናቅ ስለ ጽድቅ ተሰዶ እየለመነ ያገኘውን እየመጸወተ በጾም በጸሎት እየተጋደለ 30 ዓመት ሙሉ ተቀመጠ፡፡ በመጨረሻም ጌታችን እመቤታችንን፣ ቅዱሳን መላእክትን ሁሉ፣ ከገብረ ክርስቶስ በፊት የነበሩ ነቢያትን ሁሉ፣ ሐዋርያትን፣ ጻድቃንን፣ ሰማዕታትን ሁሉ አስከትሎ መጥቶ ቃልኪዳን ከገባለት በኋላ ከጌታችን ጋር አብረውት የመጡት ሁሉ በታላቅ ክብርና ምስጋና እያመሰገኑት ጌታችን ክብርት ነፍሱን በእቅፉ ተቀብሎ አሳርጓታል፡፡

ተአምሩ[ለማስተካከል | ኮድ አርም]

የቁስጥንጥንያው ሊቀ ጳጳሳት አባ ቴዎፍሎስ በቅዳሴ ላይ ሳሉ ከንጉሡ ቤት ሄደው የገብረ ክርስቶስን ሥጋ እንዲያመጡ የእግዚአብሔር ድምፅ ከሰማይ በትእዛዝ መጣላቸውና ሄደው ቢያዩ የገብረ ክርስቶስን ሥጋ በንጉሥ አባቱ ደጅ ወድቆ አገኙት፡፡ በገብረ ክርስቶስም እጅ ላይ በጥቅል ወረቀት የተጻፈ ደብዳቤ ነበርና ወስደው ሊያነቡት ሲሞክሩ ወረቀቱ አልላቀቅ ብሎ ፈጽሞ እምቢ አላቸው፡፡ ብዙ ምሕላና ጸሎት ከተደረገ በኋላ ወረቀቱ ከእጁ ላይ ተላቀቀና ሲነበብ ገብረ ክርስቶስ ስለ አምላኩ ፍቅር ብሎ ለ30 ዓመታት ያሳለፈውን እጅግ አሠቃቂ መከራ በተለይም በአባቱ ደጅ ማንም ሳያውቀው ያሳለፈውን እጅግ አሳዛኝ መከራና በኀዘን የሚያስለቅሰውን ታሪኩን በራሱ እጅ በዝርዝር ጽፎት ተገኝቷል፡፡ ንጉሡ አባቱና ንግሥት እናቱም ይህንን ልጃቸው የጻፈውን መልእክት ባነበቡ ጊዜ የሚሆኑት ጠፋቸው፡፡ በጣም የሚገርመው ደግሞ ወላጆቹ ሚስት አድርገው ያመጡለት የሮሙ ንጉሥ ሴት ልጅ ለባሏ ታማኝ ሆና 30 ዓመት ሙሉ በእናት አባቱ ቤት በትዕግስት ስትጠብቀው መኖሯ ነው፡፡ እርሷም ታሪኩ ሲነበብ ብትሰማ እንደ ዕብድ ሆነች፡፡ የቅዱስ ገብረ ክርስቶስን ሥጋውን ወደ ቤተ ክርስቲያን ሲወስዱ እጅግ አስገራሚ ተአምራት በድውያን ሕመምተኞች ላይ ተፈጽሟል፡፡ ከተአምራቱ የተነሣ መንገዱ በሕዝብ ተጨናንቆ አላሳልፍ ቢላቸው ንጉሡ በመንገድ ዳር ወርቅ እየበተነ ሰው ወርቁን ለማንሳት ሲሄድ በፍጥነት ወደ ቤተ ክርስቲያን አድርሰውታል ፡፡

ከገድለ ገብረክርስቶስ የተወሰዱ ጥንታዊ ስዕሎች[ለማስተካከል | ኮድ አርም]

ማጣቀሻ[ለማስተካከል | ኮድ አርም]

  1. ^ Budge, Wallis. The lives of Mabâ' Sĕyôn and Gabra Krĕstôs. The Ethiopic texts ed. with an English translation and a chapter on the illustrations of Ethiopic mss. (1898)
  2. ^ ገድለ ገብረክርስቶስ