የኢትዮጵያ አየር መንገድ በረራ 961
(ከበረራ ቁጥር 961 የተዛወረ)
በረራ ቁጥር 961 ንብረትነቱ የኢትዮጵያ አየር መንገድ የሆነ ቦይንግ 767-260ER አውሮፕላን ኅዳር ፲፬ ቀን ፲፱፻፹፱ ዓመተ ምሕረት ከአዲስ አበባ ወደ ናይሮቢ ሲሄድ ተጠልፎ ነበር። አገልግሎቱ ከቦምቤይ-አዲስ አበባ-ናይሮቢ-ብራዛቪል-ሌጎስ-አቢጃን ነበር። ይህ የአውሮፕላን ጠለፋ የተደረገው አውስትራልያ የፖለቲካ ጥገኝነት በሚፈልጉ ሦስት ኢትዮጵያውያን ነበር።
አውሮፕላኑ የህንድ ውቅያኖስ ላይ ሲሸልስ ደሴት አካባቢ ሲደርስ በነዳጅ እጥረት ምክንያት ተከሰከሰ። በዚህም ጠላፊዎቹን ጨምሮ ከ175 ተሳፋሪ መንገደኞች እና የአውሮፕላን ሰራተኞች ውስጥ 125 ለሞት ተዳርገዋል። 50 የሚሆኑት ከጉዳት ጋር ለመትረፍ ችለዋል። ይህ አደጋ በደረሰበት ጊዜ አደጋው ከፍተኛ አሰቃቂ አደጋ በመሆን 2ኛ ሁኖ ተመዝግቧል[1]።
ይዩ[ለማስተካከል | ኮድ አርም]
ማጣቀሻ[ለማስተካከል | ኮድ አርም]
- ^ "Corrections." The New York Times. November 27, 1996. Retrieved on August 19, 2014.
ድር ጣቢያ[ለማስተካከል | ኮድ አርም]
- (እንግሊዝኛ) Final Accident Report( Archived ሴፕቴምበር 24, 2015 at the Wayback Machine) - የኢትዮጵያ ሲቪል ኤቪዬሽን ባለሥልጣን
- (እንግሊዝኛ) The Hijacking of Ethiopian Airlines Flight 961 (Criminal Acts Against Civil Aviation - 1996, FAA)