ታደሰ ታምራት

ከውክፔዲያ
ታደሰ ታምራት

ፕሮፌሰር ታደሰ ታምራትአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ፣ የታሪክ ክፍል ለ30 አመታት በመስራት በ1992ዓ.ም. ጡረታ የወጡ ጸሐፊ ናቸው። በዚያው ዩኒቨርሲቲ የኢትዮጵያ ጥናት ዳይሬክተርና የህብረተሰብ ጥናት ኮሌጅ ዲን በመሆን እንዲሁም የአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ፕሬስ ኤዲተርና ዳይሬክተር በመሆን አገልግለዋል። እንዲሁም በተለያዩ የአሜሪካን ዩኒቨርስቲወች፡ UCLA (1973 እ.ኤ.አ)፣ Bucknell (1973-75); Northwestern (1975-76) እና UIUC (1992-93) በአስተማሪነት ሰርተዋል። በፈረንሳይ አገርና በእንግሊዝ አገር የተለያዩ ንግግሮችንና ሽልማቶችን ያገኙ ሲሆን በአሁኑ ወቅት ከነቤተሰባቸው በቺካጎሰሜን አሜሪካ ይኖራሉ። [1]

ታደሰ ከሚታወቁባቸው ስራወቻቸው ውስጥ Church and State in Ethiopia: 1270 - 1527 የተሰኘው መጽሐፍ በዋናነት ይጠቀሳል።

ማጣቀሻ[ለማስተካከል | ኮድ አርም]

  1. ^ "Archive copy". Archived from the original on 2012-01-14. በ2011-02-26 የተወሰደ.