አላህ

ከውክፔዲያ

በአረቢኛ ድምጽ ያላቸው “ተነባቢ ፊደላት”sound letters” 28 ሲሆኑ “አጫዋች ፊደል”stretch letter” ደግሞ 1 ሲሆን እርሱም “አሊፍ” ا ነው። በመካከላቸው ስናነባቸው የሚቀጥን ፊደል 19 ሲሆን “ተርቂቅ” ይባላል፣ የሚወፍር ፊደል ደግሞ 7 ሲሆን “ተፍሂም” ይባላል፣ ነገር ግን ተርቂቅና ተፍሂም የሆኑ ሁለት ሃርፎች “ራ” ر እና “ላም”ل ናቸው፤ “ራ” ر በፈትሃና በደማ ይወፍራል በከስራ ይቀጥናል፣ “ላም” ل ደግሞ በለፍዙል ጀላላ ማለትም በአላህ ስም ላይ ትወፍራለች። ይህንን እሳቤ ይዘን የአላህ ስምን ስናጠና “አሏህ” ٱللَّه የሚለው ስም 2699 ጊዜ በቁርአን የመጣ ሲሆን ትርጉሙ “የሚመለክ” ወይም “አምልኮ የሚገባው” ማለት ነው፤ አላህ ኢስሙል ዛት” ማለትም “የህላዌው ስም” ነው፤ “ዛት” ذات ማለት “ምንነት” ሲሆን አላህ በምንነቱ የሚመለክ ነው፤ ይህ ስም በሙያ እንዲህ ተቀምጧል፤ “ኢዕራብ” إﻋﺮﺍﺏ ማለት “ሙያ”case” ማለት ሲሆን ይህ ሙያ “ፈትሐ” فَتْحَة “ከስራ” كَسْرَة “ደማ” ضَمَّة በሚባሉ አጭር አናባቢ ሃርፎች ላይ ያገለግላሉ፦ “መንሱብ”፦ በፈትሐ የሚያገለግለው ሙያ “መንሱብ” المنصوب ማለትም ተሳቢ ሙያ”accusative case” ሲሆን አሏህ በፈትሐ ስንጠቀም “አሏሀ” اللَّهَ ይሆናል። “መጅሩር”፦ በከስራ የሚያገለግለው ሙያ “መጅሩር” المجرور ማለትም አገናዛቢ ሙያ”genitive case” ሲሆን አሏህ በከስራ ስንጠቀም “ሊሏሂ” اللَّهِ ይሆናል። “መርፉዕ”፦ በደማ የሚያገለግለው ሙያ ደግሞ “መርፉዕ” المرفوع ማለትም ባለቤት ሙያ”nominative case” ሲሆን አሏህ በደማ ስንጠቀም “አሏሁ” اللَّهُ ይሆናል። ለምሳሌ፦ “አሏሁ-ማ” ٱللَّهُمَّ ማለት “ያ-አሏህ” ياالله ማለት ነው።

ይህ ስም የፈለግነውን ሃርፍ ከላዩ ላይ ቢቀነስ ትርጉም አለው፦ @ አሏህ በሚለው መነሻ የመጀመሪያውን አንድ ሀርፍ ስንቀንሰው “ሊሏህ” لله የሚል ይሆናል፡፡ ትርጉሙም “የአላህ” ማለት ነው። @ አሏህ በሚለው የመጀመሪያዎቹን ሁለት ሃርፎች ስንቀንሰው ደግሞ ውጤቱ “ለሁ” لَهُ የሚል ይሆናል፡፡ ትርጉሙም “የእርሱ” የሚል ነው፡፡ @ አሏህ በሚለው የመጀመሪያዎቹን ሶስት ሃርፎች ስንቀንሰው ደግሞ ውጤቱ “ሁ” هُ የሚለው ይሆናል፡፡ ትርጉሙም “እርሱ” የሚል ነው፡፡ @ አሏህ በሚለው ሀርፎች ከመሀል ከሁለቱ የላም ሃርፎች አንዱን ስንቀንሰው ውጤቱ “ኢላህ” إِلَٰه የሚለው ይሆናል፤ ትርጉሙ “አምላክ” ማለት ነው፤ “ኢላህ” የሚለው ቃል 147 ጊዜ በቁርአን የመጣ ሲሆን ተባታይ ነው፤ አንስታይ ሲሆን ደግሞ “ኢላሃህ” إلاهة ነው፤ የኢላህ ብዙ ቁጥር ደግሞ “አሊሀህ” آلِهَةٌ ነው፤ “ኢላህ” በተለያየ አገናዛቢ ተውላጠ ስም ላይ ሲመጣ፦ “ኢላሂ” إِلَٰهي “አምላኬ” “ኢላሁና” إِلَٰهُنَا “አምላካችን” “ኢላሀከ” إِلَٰهَكَ “አምላክህ” “ኢላሀኩም” إِلَٰهُكُمْ “አምላካችሁ” “ኢላሀሁ” إِلَٰهَهُ “አምላኩ” “ኢላሀሁም” إِلَٰهَهُمْ “አምላካቸው” ይሆናል። “ኢላህ” ማለት “አምላክ” ተብሎ በትርጉም መጠቀም ይቻላል፤ ግን “አላህ” የተፀውዖ ስም ስለሆነ እራሱ ነው የሚቀመጠው፦ 17:22 “ከአላህ” ጋር ሌላን “አምላክ” አታድርግ፤ የተወቀስክ ረዳት የሌለህ ትሆናለህና لَّا تَجْعَلْ مَعَ ٱللَّهِ إِلَٰهًا ءَاخَرَ فَتَقْعُدَ مَذْمُومًۭا مَّخْذُولًۭا ፤ 28:88 “ከአላህም” ጋር ሌላን “አምላክ” አትጥራ وَلَا تَدْعُ مَعَ ٱللَّهِ إِلَٰهًا ءَاخَرَ ۘ لَآ إِلَٰهَ إِلَّا هُوَ ۚ كُلُّ شَىْءٍ هَالِكٌ إِلَّا وَجْهَهُۥ ۚ لَهُ ٱلْحُكْمُ وَإِلَيْهِ تُرْجَعُونَ ፡፡ 26:213 “ከአላህም” ጋር ሌላን “አምላክ” አትጥራ፤ ከሚቀጡት ትኾናለህና فَلَا تَدْعُ مَعَ ٱللَّهِ إِلَٰهًا ءَاخَرَ فَتَكُونَ مِنَ ٱلْمُعَذَّبِينَ ፡፡

አሏህ በዕብራይስ አሁንም “ላሜድን” ל ተሽዲድ ስናደርገው “አሏህ” אללה‎‎ ሲሆን ከውስጡ ሁለት “ላሜድ” ל ሲኖረው አንዱን ስንቀንስ እና በፈትሃ ስንጨርሰው “ኤሎሃ” אלוהּ ይሆናል፤ ትርጉሙም “አምላክ” ማለት ነው፤ የኤሎሃ ብዜት ደግሞ “ኤሎሂም” אלהים ነው፤ “ኤል” אֵל የኤሎሃ ምፃረ-ቃል ሲሆን የኤል ብዜት ደግሞ “ኤሊም” אֵלִ֑ים ነው፤ “ያ-አሏህ” יַאלְלָה “አሏህ ሆ” እና “ወ-ሏህ” וַאלְלָה “በአሏህ” ይባላል። አሏህ በአረማይክ አሁንም “አሏህ” ܐܲܠܵܗܵܐ ሲሆን ከውስጡ “ኤላህ”ܐܠܗܐ ማለትም “አምላክ” የሚል ቃል አለ፤ ዋቢ መጽሐፍት፦ 1. Bergsträsser, Gotthelf. 1995. Introduction to the Semitic Languages: Text Specimens and Grammatical Sketches. 2. Fitzmyer, J. (1997), The Semitic Background of the New Testament, Eerdmans Publishing. 3. Bennett, Patrick R. 1998. Comparative Semitic Linguistics: 4. Moscati, Sabatino. 1969. An introduction to the comparative grammar of the Semitic languages: phonology and morphology.

እንግዲህ ኢየሱስ፣ ሔኖክ፣ ኖህ እና አብርሐም የሚጠቀሙበት ዘዬ አረማይክ ከነበረ እና ሌሎች የእስራኤል ነብያት የዕብራይስጥ ዘዬ ሲጠቀሙ ከነበረ “አሏህ” የሚለውን ስም መጠቀማቸው ግድ ይላል፤ ነገር ግን አሁን በዘመናችን የአላህ ጥንታዊ ነቢያት የተሰጣቸው ኪታባት የተዋቀረበት አንጓ፣ የተናገሩበት ቋንቋ፣ የመልዕክቱ ምጥቀት ሆነ የቃላቱ ልቀት በዘመናችን እንደሌሉ የታሪክ ምሁራን ያትታሉ፣ ለምሳሌ የእስራኤል ልጆች ውስጥ የነበሩት ነቢያት ሲናገሩበት የነበረው ቋንቋ ዕብራይስጥ ሲሆን እነርሱ የተናገሩበት መጽሐፍት የሉም፣ በጣም ቀደምትነት አለው የሚባለው የነቢያት መጽሐፍት ግልባጭ በግሪክ ሰፕቱአጀንት የተዘጋጀው ሲሆን ከሰፕቱአጀንት በኋላ የተዘጋጁት የሙት ባህር ጥቅል፣ ማሶሬቲክ፣ ሰመሪያን ይህንኑ የግሪኩን መሰረት አድርገው ነው የተተረጎሙት፣ ከሰፕቱአጀንት በፊት የነበረው የነቢያት መጽሐፍት ዛሬ የለም፣ ከሌለ አላህ የሚለው ቃል ይጠቀሙ አይጠቀሙ ምንም ምንጭ የለም ማለት ነው፣ ወደ ኢየሱስም ስንመጣ ኢየሱስ ሲናገርበት የነበረ ቋንቋ አረማይክ ሲሆን ሃዋርያቱም ሲናገሩበት የነበረው ይህን ቋንቋ ነው፣ ነገር ግን ወደ ሁለተኛው ትውልድ ይህ የኢየሱስ ትምህርት ሲገባ የተጻፈው ኮይኔ በሚባል የግሪክ ቋንቋ ነው፣ ስለዚህ ነቢያት አምላካቸውን ማን ብለው እንደነበር የሚያሳይ የቋንቋ መረጃ በዛሬ ጊዜ የለም። አላህ የሚለውን ስም ነቢያቶች ተናግረውት አያውቁም የሚለው አሉባልታ ምንጭ አልባና ሰነድ አልባ ነው፣ ይህን ደፍሮ ለመናገር ስረ-መስረት ያለው አንጓ፣ ቋንቋ፣ ምጥቀት ሆነ ልቀት ያስፈልጋል፣ በተረፈ “”እግዚአብሔር፣ ቴኦስ፣ ጋድ፣ ጉድ”” የሚሉት ቃላት ባዕደ-ቃላት እና ኢላህ ለሚለው ቃል ትርጉም ናቸው እንጂ አሏህ ለሚለው ቃል ትርጉም አይደሉም።

አላህ ጥንት ነቢያቶች የሚያመልኩት የነቢያት አምላክ መሆኑን የምናውቀው ከጥንቶቹ ነቢያት ጋር የነበረውን መስተጋብር ለመግለጽ፦ “ቁልና” قُلْنَا *አልን* ፣ “አርሰልና” أَرْسَلْنَا*ላክን*፣ “አውሃይና” أَوْحَيْنَا *አወረድን* በማለት ጥንትም ነቢያትን ሲልክ የነበረው፣ ግልጠተ-መለኮት*Revelation* ሲያወርድ የነበረውና በተለያየ መንገድ ሲያናግራቸው የነበረው እርሱ መሆኑን ይገልጻል፦

1. አልን፦ 20:116 ለመላእክትም፣ ለአዳም ስገዱ፣ *ባልን* ጊዜ አስታውስ፤ 2:35 «አደም ሆይ! አንተ ከነሚስትህ በገነት ተቀመጥ፤ ከርሷም በፈለጋችሁት ስፍራ በሰፊው ተመገቡ፤ ግን ይህችን ዛፍ አትቅረቡ፤ ከበደለኞች ትኾናላችሁና» *አልንም*፡፡ 11:40 ትእዛዛችንም በመጣና እቶኑም በገነፈለ ጊዜ፣ በርሷ ውስጥ ከየዓይነቱ ሁሉ ሁለት ሁለት፣ ወንድና ሴት ቤተሰቦችህንም ቃል ያለፈበት ብቻ ሲቀር ያመነንም ሰው ሁሉ ጫን *አልነው*፤ 22:26 ለኢብራሂምም የቤቱን ስፍራ መመለሻ ባደረግንለት ጊዜ፣ በኔ ምንንም አታጋራ፤ ቤቴንም፣ ለሚዞሩትና ለሚቆሙበት፣ ለሚያጎነብሱትና በግንባራቸውም ለሚደፉት ንጹሕ አድርግላቸው፣ *ባልነው* ጊዜ አስታውስ። 2:125 ወደ ኢብራሂምና ወደ ኢስማዒልም ቤቴን ለዘዋሪዎቹና ለተቀማጮቹም ለአጎንባሾች ሰጋጆቹም አጥሩ *ስንል* ቃል ኪዳን ያዝን፡፡ 2:60 ሙሳም ለሕዝቦቹ መጠጥን በፈለገ ጊዜ የኾነውን አስታውሱ፡፡ «ድንጋዩንም በበትርህ ምታ» *አልነው*፡፡ 17:2 ሙሳንም መጽሐፉን ሰጠነው፤ ለእስራኤልም ልጆች መሪ አደረግነው፤ ከኔ ሌላ መጠጊያን አትያዙ *አልናቸውም*።

2. ላክን፦ 16:36 በየሕዝቡም ሁሉ ውስጥ አላህን ተገዙ፤ ጣዖትንም ራቁ፤ በማለት መልክተኛን በእርግጥ *ልከናል*፤ 57:25 መልክተኞቻችንን በግልጽ ማስረጃዎች በእርግጥ *ላክን*፤ 23:32 በውስጣቸውም ከእነሱ የኾነን መልክተኛ አላህን ተገዙ ከእርሱ በቀር ሌላ አምላክ የላችሁም አትጠነቀቁምን በማለት *ላክን*፡፡ 7:59 ኑሕን ወደ ወገኖቹ በእርግጥ ላክነው፤ 11:50 ወደ ዓድም ወንድማቸውን ሁድን ላክን፤ 11:61 ወደ ሠሙዶችም ወንድማቸውን ሷሊህን ላክን፤ 11:84 ወደ መድየንም ወንድማችውን ሹዐይብን፣ ላክን፤

3. አወረድን፦ 4:163 እኛ ወደ ኑሕና ከርሱ በኋላ ወደ ነበሩት ነቢያት *እንዳወረድን*፣ ወደ አንተም *አወረድን*፤ ወደ ኢብራሂምም፣ ወደ ኢስማዒልም፣ ወደ ኢስሐቅም፣ ወደ ያዕቆብም፣ ወደ ነገዶቹም ወደ ዒሳም፣ ወደ አዮብም፣ ወደ ዩኑስም፣ ወደ ሀሩንና ወደ ሱለይማንም *አወረድን*፤ ለዳዉድም ዘቡርን ሰጠነው። 21:25 ከአንተ በፊትም፣ እነሆ ከኔ ሌላ አምላክ የለምና ተገዙኝ፣ በማለት ወደርሱ *የምናወርድለት* ቢሆን እንጅ ከመልክተኛ አንድንም አልላክንም። 12:109 ካንተ በፊትም ከከተሞች ሰዎች ወደ እነርሱ ራዕይ *የምናወርድላቸው* የሆኑን ወንዶችን እንጂ አልላክንም፤ 21:7 ከአንተም በፊት ወደ እነርሱ *የምናወርድላቸው* የኾኑ ሰዎችን እንጂ ሌላን አልላክንም፤ 16:43 ከአንተም በፊት ወደ እነርሱ ወሕይን *የምናወርድላቸውን* ሰዎችን እንጂ፣ ሌላን አልላክንም፤

አላህ የነቢያት አምላክ ነው፤ ኑሕ፣ ሁድ፣ ሷሊህ፣ ኢብራሒም፣ ሹዐይብ፣ ሙሳ እና ኢሳ አላህ እያሉ ይጠቀሙ እንደነበር ቃሉ ይነግረናል፦ 16:36 በየሕዝቡም ሁሉ ውስጥ “አላህን” አምልኩ፤ ጣዖትንም ራቁ፤ በማለት መልክተኛን በእርግጥ ልከናል፤

“ኑሕ” 11:25-26 ኑሕንም ወደ ሕዝቦቹ በእርግጥ ላክን፤ አላቸውም ፦ እኔ ለናንተ ግልጽ አስፈራሪ ነኝ። አላህን እንጂ ሌላን አትገዙ፤ እኔ በናንተ ላይ የአሳማሚን ቀን ቅጣት እፈራላችኋለሁና።

“ሁድ” 11:50 ወደ ዓድም ወንድማቸውን ሁድን ላክን አላቸው ፦ ወገኖቼ ሆይ አላህን ተገዙ ከእርሱ ሌላ ምንም አምላክ የላችሁም፤ እናንተም ቀጣፊዎች እንጂ ሌላ አይደላችሁም።

“ሷሊህ” 11:61 ወደ ሠሙዶችም ወንድማቸውን ሷሊህን ላክን፤ ፦ሕዝቦቼ ሆይ አላህን ተገዙ፤ ከርሱ ሌላ ለናንተ አምላክ፣ የላችሁም፤ .. አላቸው።

“ኢብራሒም” 19:48 እናንተንም ከአላህ ሌላ የምትግዙትንም እርቃለሁ፤ ጌታየንም እግዛለሁ፤ ጌታየን በመገዛት የማፍር አለመኾኔን እከጅላለሁ።

“ሹዐይብ” 11:84 ወደ መድየንም ወንድማችውን ሹዐይብን፣ ላክን፤ አላቸው ሕዝቦቼ ሆይ! አላህን ተገዙ፤ ከርሱ ሌላ ለናንተ አምላክ የላችሁም፤ ስፍርንና ሚዛንንም አታጉድሉ፤ እኔ በጸጋ ላይ ሆናችሁ አያችኋለሁ፤ እኔም በናንተ ላይ የከባቢን ቀን ቅጣት እፈራለሁ።

“ሙሳ” 7:104-105 ሙሳም አለ፦ፈርኦን ሆይ! እኔ ከዓለማት ጌታ የተላክሁ መልክተኛ ነኝ፤ በአላህ ላይ ከእውነት በቀር አለመናገር ተገቢዬ ነው፤ ከጌታችሁ በታምር በእርግጥ መጣኋችሁ፤ የእስራኤልንም ልጆች ከኔ ጋር ልቀቅ።

ኢሳ” 3:51 አላህ ጌታየና ጌታችሁ ነዉ፤ ስለዚህ ተገዙት፤ ይህ ቀጥተኛ መንገድ ነዉ አላቸዉ።

ነጥብ ሶስት “አሏህና ታሪካዊ ፍሰት” አሏህ የሚለው ስም ነብያችን ነብይ ሆነ ከመላካቸው በፊትና ቁርአን ከመውረዱ በፊት በሴመቲክ ዳራ ደግሞ ከሁሉ በላይ የሆነው አንዱ አምላክ ሲጠራበት የነበረ ስም እንደነበር የተለያየ መድብለ-እውቀቶች*Encycolopedias* ሆኑ ታሪካዊ ፍሰቶች ያትታሉ፦ 1. የሃይማኖት መድብለ-እውቀት 1987: “አላህ የሚለው ስም ስረ-መሰረት የጋራ በሆኑ በተለያዩ ጥንታዊ የሴም ቋንቋዎች ይገኛል” ገጽ 27. Encycolopedia of religion 1987: “the orgin of Allah is found in a root common to various ancient semetic languages” p27. 2. የክርስትና መድብለ-እውቀት 2001: “ ቅድመ-ቁርአን አረብ ተናጋሪ ክርስቲያንና አይሁድ እንዲሁ አላህ ለታላቁ አምላክ ይጠቀሙበት ነበር” ገጽ 101. Encyclopedia of Christianity 2001: “before Quran Arabic-speaking Christians and Jews also refer to supreme God as Allāh” page 101. 3. የኢስላም መድብለ-እውቀት 1913: “አረቦች ቅድመ-ነቢዩ ሙሃመድ በነበሩት ዘመናት አላህ የሚባል ታላቅ አምላክ ያመልኩ ነበር” ገጽ 302. Encyclopedia of Islam 1913: “Before prophet Muhammad Arabian was worshiping supreme God who is Allah” page 302. 4. የብሪታኒካ መድብለ-እውቀት 1996: “ቅድመ-ቁርአን በነበሩት አረቢያን መጽሐፍት ውስጥ አላህ የሚለው ቃል ይገኛል” ገጽ 106. Encyclopedia of britannica 1996: “Before Quran The word Allah was in the Arabic books” page 106.

አላህ እና ጣዖታት አንድን እምነት ለማመን ቅድሚያ ስለዚያ እምነት በቂ እውቀት ይጠይቃል፤ በመሃይምነት እውር ድንብር የሆነ ፀለምተኛ እምነት መከልተል በኢስላም አይሰራም፦ 17፥36 ለአንተም በእርሱ #እውቀት #የሌለህን ነገር #አትከተል፤

የእውቀት መጀመሪያ ደግሞ የፈጠረንን ፈጣሪያችንን ማወቅ ነው፤ በኢስላም የመጀመሪያው እርምጃ “ከአላህ ሌላ አምላክ አለመኖሩ” ማመን ሳይሆን “ከአላህ ሌላ አምላክ አለመኖሩን” ማወቅ ነው፦ 47:19 እነሆ “ከአላህ ሌላ አምላክ” لَا إِلَٰهَ إِلَّا اللَّهُ አለመኖሩን #እወቅ፤

"ላ ኢላሃ ኢለ ሏህ"  لَا إِلَٰهَ إِلَّا اللَّهُ  "ከአሏህ በቀር ሌላ አምላክ የለም" ማለት ነው፣ ጣኦታትን የምንክድበት፣  ከአላህ ሌላ በሃቅ ሊመለክ የሚችል አምላክ አለምኖሩን የምናምንበት ቃለ-ምስክርነት ነው፦

2:256 ከጠማማው በእርግጥ ተገለጠ፡፡ #በጣዖትም "የሚክድ" እና #በአላህ "የሚያምን" ሰው ለርሷ መበጠስ የሌላትን ጠንካራ ዘለበት በእርግጥ ጨበጠ፡፡ 39:17 እነዚያም #ጣዖትን "የሚያመልኳት" يَعْبُدُوهَا ከመሆን የራቁ ወደ #አላህም የዞሩ ለእነርሱ #ብስራት አላቸው፤ ስለዚህ ባሮቼን አብስር ። 43፥26-27 ኢብራሂምም ለአባቱ እና ለሕዝቦቹ ባለ ጊዜ አስታውስ፦ "እኔ ከምታመልኩት ሁሉ #ንጹሕ ነኝ፤ ከዚያ #ከፈጠረኝ #በቀር #አላመልክም እርሱ በእርግጥ ይመራኛልና"። 16:36 በየሕዝቡም ሁሉ ውስጥ "#አላህን #አምልኩ #ጣዖትንም #ራቁ" በማለት መልክተኛን በእርግጥ ልከናል፤

ይህ ቃለ-ምስክርነት በቁርአን "ጠንካራን ዘለበት" ይባላል፦ 31:22 እርሱ መልካም ሠሪ ሆኖ ፊቱን وَجْهَهُ ወደ አላህ የሚሰጥም يُسْلِمْ ሰው፣ #ጠንካራ #ገመድ بِالْعُرْوَةِ በእርግጥ ጨበጠ፤ የነገሩም ሁሉ ፍጻሜ ወደ አላህ ነው። 2:256 በጣዖትም የሚክድና በአላህ የሚያምን ሰው ለርሷ መበጠስ የሌላትን #ጠንካራ #ዘለበት بِالْعُرْوَةِ በእርግጥ ጨበጠ፡፡ አላህም ሰሚ ዐዋቂ ነው፡፡

ይህ ቃለ-ምስክርነት ሁለት ማዕዘናት አለው፤ አንደኛው ነፍይ ሲሆን ሁለተኛ ኢሥባት ነው፤ ይህንን እሳቤ ነጥብ በነጥብ እንመልከት፦

ነጥብ አንድ "ነፍይ" "ነፍይ" نفي ማለት "አፍራሽ" ሲሆን አሉታዊ ቃል ነው፤ ይህም አሉታዊ ቃል፦ "ላ ኢላሃ" لَا إِلَٰهَ "ሌላ አምላክ የለም" ብለን ስንል ማንኛውንም ጣኦታት ውድቅ የምናደርግበት ነው፤ በቁርአን ከአላህ ውጪ የሚደረግ ባዕድ አምልኮ "ጣኡት" لطَّاغُوتِ ፣ "አውሳን" أَوْثَٰن እና "አስናም" أَصْنَام ይባላሉ፣ እነዚህ ጣኦታት ከዓለማቱ ጌታ ሌላ የሚመለኩ ምንነትና ማንነት ናቸው፤ እጅጉን ከዓለማቱ ጌታ ከአላህ ተለይተው ተቀምጧል፦ 1. "ጣኡት" 2:256 #በጣዖትም لطَّاغُوتِ የሚክድና በአላህ የሚያምን ሰው ለርሷ መበጠስ የሌላትን ጠንካራ ዘለበት በእርግጥ ጨበጠ፡፡ 4:76 እነዚያ ያመኑት ሰዎች፣ በአላህ መንገድ ይጋደላሉ፤ እነዛ የካዱትም #በጣዖት لطَّاغُوتِ መንገድ ይጋደላሉ፤ 16:36 በየሕዝቡም ሁሉ ውስጥ አላህን አምልኩ #ጣዖትንም لطَّاغُوتِ ራቁ፤ በማለት መልክተኛን በእርግጥ ልከናል፤

2."አውሳን" 29:17 ከአላህ ሌላ የምታመልኩት #ጣዖታትን أَوْثَانًا ብቻ ነው፤ ውሸትንም ትቀጣጥፋላችሁ፤ እነዚያ ከአላህ ሌላ የምታመልኩአቸው ለእናንተ ሲሳይን ሊሰጧችሁ አይችሉም፤ 29:25 ኢብራሂም አለም፦ ከአላህ ሌላ #ጣዖታትን أَوْثَانًا አማልክት የያዛችሁት በቅርቢቱ ሕይወት በመካከላችሁ ለመዋደድ ብቻ ነው፤ ከዚያም በትንሣኤ ቀን ከፊላችሁ በከፊሉ ይክዳል፤ ከፊላችሁም ከፊሉን ይረግማል፤ መኖሪያችሁም እሳት ናት፤ ለእናንተም ከረዳቶች ምንም የላችሁም።

3. "አስናም" 6:74 ኢብራሒምም ለአባቱ ለአዘር «#ጣዖታትን أَصْنَامًا አማልክት አድርገህ ትይዛለህን እኔ አንተንም ሕዝቦችህንም በግልጽ መሳሳት ውስጥ ኾናችሁ አያችኋለሁ» ባለ ጊዜ አስታውስ. 21:57 በአላህም ስም እምላለሁ ዟሪዎች ሆናችሁ ከኼዳችሁ በኋላ #ጣዖቶቻችሁን أَصْنَامًا ተንኮል እሰራባቸዋለሁ፣ አለ። 14:35 ኢብራሂምም ባለ ጊዜ አስታውስ ፦ ጌታዬ ሆይ! ይህንን አገር ጸጥተኛ አድርገው፤ እኔንም ልጆቼንም #ጣዖታትን أَصْنَامًا ከማምለክ አርቀን፤

ነጥብ ሁለት "ኢሥባት" "ኢሥባት" إثبات ማለት "ማፅደቅ" ሲሆን አውንታዊ ቃል ነው፤ ይህም አውንታዊ ቃል፦ "ኢለ ሏህ” إِلَّا اللَّهُ "ከአላህ በቀር" ብለን ስንል አንዱን አምላክ በብቸኝነትና በእውነት ልናመልከው የምናፀድቅበት ነው፤ አንዱ እምላክ አላህ ነገሮችን ካለመኖር ወደመኖር የፈጠረ፣ የሚያሞት ህያው የሚያደርግ፣ መጥቀምና መጉዳት የሚችል፣ ሁሉን የሚያውቅ፣ ሁሉን የሚያይ፣ ሁሉን የሚሰማና በእኔነት የሚናገር ነው፦ 1. "ሁሉን የፈጠረ ነው" 46:4 #ከአላህ ሌላ የምታመልኳቸው አያችሁን? ከምድር ምንን እንደ #ፈጠሩ# አሳዩኝ ወይም በሰማያት ለእነርሱ መጋራት አላቸውን? 50:38 ሰማያትንና ምድርን በመካከላቸው ያለውንም ሁሉ በስድስት ቀናት ውስጥ በእርግጥ #ፈጠርን፡፡ 49:13 እላንተ ሰዎች ሆይ እኛ ከወንድና ከሴት #ፈጠርናችሁ፤ እንድትተዋወቁም ጎሳዎችና ነገዶች አደረግናችሁ፤

2. "የሚያሞት ህያው የሚያደርግ ነው" 30:40 አላህ ያ የፈጠራችሁ፣ ከዚያም ሲሳይን የሰጣችሁ፣ ከዚያም #የሚያሞታችሁ#፥ ከዚያም #ሕያው# የሚያደርጋችሁ ነው፤ ከምታጋሩዋቸው ጣዖታት ውስጥ ከዚኻችሁ አንዳችን የሚሠራ አልለን? 44:8 ከእርሱ ሌላ አምላክ የለም፤ #ሕያው ያደርጋል#፣ #ያሞታልም፣ ጌታችሁ፣ የመጀመሪያ አባቶቻችሁም ጌታ ነው።

3. "መጥቀምና መጉዳት የሚችል ነው" 20:89 ወደ እነነሱ ንግግርን የማይመልስ ለእነርሱም #ጉዳትንና #ጥቅምን የማይችል መሆኑን አያዩምን? 10:106 ከአላህም በቀር #የማይጠቅምንና #የማይጎዳን አታምልክ፡፡ ብትሠራም አንተ ያንጊዜ ከበደለኞቹ ትሆናለህ» ተብያለሁ" በላቸው፡፡ 5:76 ከአላህ ሌላ ለእናንተ #መጉዳትንና #መጥቀምን የማይችልን ታመልካለህን? በላቸው፤

4. "ሁሉን የሚያውቅ ነው" 60:1 #እኔ የምትደብቁትንና የምትገልጹትን #የማውቅ ስሆን ወደ እነርሱ በፍቅር ትመሣጠራላችሁ፤ 64:4 በሰማያትና በምድር ውስጥ ያለውን ሁሉ ያውቃል፤ የምትደብቁትንም የምትገልጡትንም ያውቃል አላህ በልቦች ውስጥ ያለውን ሁሉ ዐዋቂ ነው።

5. "ሁሉ ተመልካች ነው" 34:11 #እኔ የምትሠሩትን ነገር ሁሉ ተመልካች ነኝና። 57፥4 #አላህም የምትሠሩትን ሁሉ ተመልካች ነው።

6. "ሁሉን የሚሰማ ነው" 2:186 ባሮቼም ከእኔ በጠየቁህ ጊዜ፡- እኔ ቅርብ ነኝ፡፡ የለማኝን ጸሎት በለመነኝ ጊዜ #እቀበለዋለሁ፡፡ ስለዚህ ለኔ ይታዘዙ፤ በእኔም ይመኑ፤ እነርሱ ሊመሩ ይከጀላልና፡፡ 9:103 ለእነርሱም ጸልይላቸዉ፤ ጸሎትህ ለእነርሱ እርካታ ነዉና አላህም "ሰሚ" ዐዋቂ ነው።

7. "እኔነት ያለው ተናጋሪ ነው" 21:92 "#እኔም" ጌታችሁ #ነኝ እና "አምልኩኝ"። 2:160 እነዚህም በእነርሱ ላይ ጸጸታቸውን እቀበላለሁ፤ #እኔም ጸጸትን በጣም ተቀባይ አዛኙ #ነኝ፡፡

ነብያችን"ﷺ" ወደ መካ ሲገቡ በካዕባህ የሚመለኩ 360 ጣዖታትን ሰባብረዋል፤ ያስቀሩት አንድም ጣዖት የለም፤ አል-ሐጀሩል አስወድ ከ 360 ጣዖታት መካከል ነበር የሚለው ዲስኩር የሚሽነሪዎች ቅጥፈት እንጂ የታሪክ ሆነ የሥነ-ቅርስ መረጃ የለም፤ ሐጀሩል አስወድ መጉዳትንና መጥቀምን የማይችልና የአላህን ቤት መዞር የሚጀመርበት መነሻ ነጥብ እንጂ አምልኮ የሚቀበል አይደለም። ይህንን ከሐዲስ መረዳት ይቻላል፦ ኢማም ቡሃሪ መጽሐፍ 25, ሐዲስ 83: ዑመር ወደ ሃጀሩል አስወድ ቀረቦ ሳመውና፦ አውቃለው #አትጠቅምም #አትጎዳም ነብዩ"ﷺ" ሲስሙህ ባላይ ኖሮ አልስምህም ነበር። عَنْ عُمَرَ ـ رضى الله عنه ـ أَنَّهُ جَاءَ إِلَى الْحَجَرِ الأَسْوَدِ فَقَبَّلَهُ، فَقَالَ إِنِّي أَعْلَمُ أَنَّكَ حَجَرٌ لاَ تَضُرُّ وَلاَ تَنْفَعُ، وَلَوْلاَ أَنِّي رَأَيْتُ النَّبِيَّ صلى الله عليه وسلم يُقَبِّلُكَ مَا قَبَّلْتُكَ‏.‏

ሃጀሩል አስወድ መስማት፣ መናገር፣ ማየት፣ ማወቅ የማይችል ህያው ያልሆነው ነገር ነውና አይጠቅምም አይጎዳም፣ የማይጠቅምና የማይጎዳ ነገር አይመለክም፤ የሚመለከው መጥቀና መጉዳት የሚችለው የሰማያትና የምድር ጌታ ብቻ ነው፦ 13:16 የሰማያትና የምድር ጌታ ማን ነው? በላቸው፤ አላህ ነው በል፤ #ለነፍሶቻቸው #ጥቅምንም #ጉዳትንም የማይችሉን ረዳቶች ከእርሱ ሌላ ያዛችሁን? በላቸው፤

የፈጣሪ ሃቅ አምልኮ፣ መለማመን፣ ስለት መሳል፣ መስገድ ወዘተ ነው፤ ይህንን ሃቅ ከመሳም ጋር ማምታታት የለብንም፤ ሲጀመር "መሳም" የመውደድ መገለጫ እንጂ በራሱ መውደድ አይደለም፤ ምክንያቱም ሳንስማቸው የምንወዳቸው ሰዎች ስላሉ፤ ሲቀጥል "መሳም" የፈጣሪ ሃቅ አይደለም፤ ፈጣሪ አይሳምምና፤ ሲሰልስ "መሳም" የፍጡራን መብት ነው፤ አንድ ሰው አባቱን ሳመ ማለት አመለከ ማለት አይደለም፤ አንድ ሰው በእግር ኳስ አሸንፎ ዋንጫ ቢስም አመለከ አይባልም፤ ለሃጅሩል አስወድ አምልኮ፣ መለማመን፣ ስለት መሳል፣ መስገድ ወዘተ ቢቀርብ ኖሮ ይህ ማሻረክ ወይም ባእድ አምልኮ ይሆን ነበር፤ ነገር ግን ይህ ፈፅሞ ሽርክ ነው፤ በኢስላም በድንጋይና በድንጋይ ላይ የሚደረግ አምልኮ "ኑሱብ" نُصُب እና "አዝላም" أَزْلَٰم ሲባል በአላህ ላይ ማሻረክ የሆነ አመፅ ነው፦ 5:90 እላንተ ያመናችሁ ሆይ! የሚያሰክር መጠጥ፣ ቁማርም፣ "አንሳብ" وَالْأَنْصَابُ "አዝላምም"* بِالْأَزْلَامِ ከሰይጣን ሥራ የሆኑ እርኩስ ብቻ ናቸው፤ እርኩስን ራቁትም ልትድኑ ይከጀላልና። 5:3 ለኑሱብ" النُّصُبِ የታረደው *በአዝላምም* بِالْأَزْلَامِ ዕድልን መፈለጋችሁ በእናንተ ላይ እርም ተደረገ ይሃችሁ "አመፅ" ነው።

ኢስላም[ለማስተካከል | ኮድ አርም]

Medallion showing "Allah" in Hagia Sophia, Istanbul, Turkey.

በእስልምና እምነት አላህ ማለት በሴማዊ ቋንቋ ውስጥ "አምልኮ የሚገባው"ፍፁም ፍጥረታትን የማይመስል፣ ከ"العرش" (ከዙፋኑ) በላይ ያለ ፣ ከፍጥረታቱ የተነጠለ፣ በአዕምሮ መንሰላሰል ሊደረስበት የማይችል ኃያል ጌታ ማለት ነው። ከነብዩ ከአደም (አ.ሰ) ጀምሮ እስከ ነብዩ ሙሃመድ (ሰ.አ.ወ) ድረስ ያሉትን በቁርአን ላይ እንደተጠቀሱት ፪፭ ሃያ አምስት እና ከዛ በላይ ያልተጠቀሱ ነብያትን የላከ አንድ እና ብቸኛ አምላክ. አላህ በቁርአን ላይ የተጠቀሱ ፱፱ (ዘጠና ዘጠኝ) ስሞች አሉት ሁሉም የሚናገሩት ስለማነነቱ እና ስለባህሪዉ ነዉ. የአላህን ለማወቅ የፈለገ ሰዉ ስሞችሁን ማስተንተን እና መረዳት ከቻለ አልላህን በመጠኑም ቢሆን ማወቅ ይችላል አሏህ መ

በቁርኣን አላህ 99 ባሕርያቱን የሚገልጹ ስሞች አሉት== አላህ ከፍጡራኑ ጋር የማይመሳሰል አስማኡል ሁስና الْأَسْمَاءُ الْحُسْنَىٰመልካም ስሞች አሉት፦ 59:24 እርሱ አላህ ፈጣሪው ከኢምንት አስገኚው ቅርጽን አሳማሪው ነው፤ ለርሱ መልካም ስሞች الْأَسْمَاءُ الْحُسْنَىٰ አሉት፤ 20:8 አላህ ከርሱ ሌላ አምላክ የለም ለርሱ መልካም የሆኑ ስሞች الْأَسْمَاءُ الْحُسْنَىٰ አሉት። 17:110 ፦አላህን ጥሩ፤ ወይም አልረሕማንን ጥሩ፤ ማንኛውንም ብትጠሩ፣ መልካም ነው፤ ለርሱ መልካም ስሞች الْأَسْمَاءُ الْحُسْنَىٰ አሉትና በላቸው፤ 7:180 ለአላህም መልካም ስሞች الْأَسْمَاءُ الْحُسْنَىٰ አሉት፤ ስትጸልዩ በርሷም ጥሩት እነዚያንም ስሞቹን የሚያጣምሙትን ተውዋቸው፤

እነዚህ 99 የባህርይ መልካም ስሞች በቁርአን የተገለጹት ናቸው እንጂ የአላህ መልካም ስሞች 99 ብቻ ናቸው ማለት አይደለም፣ ” አላህ 99 ስሞች አሉት ” ነው እንጂ ” የአላህ ስሞች 99 ናቸው ” የሚል የለም፣ ምክንያቱም ነቢያችን ራስህን በሰየምክበት፡ በመጽሐፍህም ውስጥ በጠቀስከው፡ ከፍጡሮችህም ለማንኛውም ባሳወቅከው፡ አንተ ዘንድም ብቻህን ባወቅከው ስሞችህ እለምንሀለሁ ብለዋል፦ Musnad Ahmad Book 5 number 267 It was narrated by Abdullah Ibn Mas’ud that the Prophet pbuh said: Whoever is ever afflicted by such as depression and sadness and then recites: O Allah, verily I am your servant and the son of your servant, the son of your amah (female servant), my life is in your hands, it passes in Your law, implimented as You willed, I ask of You with all the Names which is Yours, which You have named Yourself or taught anyone of your creations,or brought down in Your books, or which You have hidden by Your side in the unseen world.

በቁርአን የተገለጹ 99 ስሞች ማፈዝ፣ ማወቅ፣ ትርጉማቸውን ተረድቶ በእነዚህ ስሞች አላህን መጥራት የጀነት ያደርጋል፦ 1.ማፈዝ Sahih Bukhari, Volume 9, Book 93, Number 489: Narrated Abu Huraira: Allah’s Apostle said, “Allah has ninety-nine Names, one-hundred less one; and he who memorized them all by heart will enter Paradise.”

2.ማወቅ Sahih Bukhari, Volume 3, Book 50, Number 894: Narrated Abu Huraira: Allah’s Apostle said, “Allah has ninety-nine names, i.e. one-hundred minus one, and whoever knows them will go to Paradise.

3.ትርጉማቸውን መረዳትና መተግበር Sahih Bukhari, Volume 8, Book 75, Number 419: Narrated Abu Huraira: Allah has ninety-nine Names, i.e., one hundred minus one, and whoever believes in their meanings and acts accordingly, will enter Paradise

ነጥብ ሶስት የአላህ ስሞች የሚከተሉት ናቸው፦ 1.አል-ረሕማን፦ ሙእሚንም ካሐዲም ለሆኑ ፍጡራን እዝነቱ ሰፊና ትልቅ:: 1.1 2.አር-ረሒም፦ ለሙእሚኖች በተለየ ሁኔታ በጎ ዋይ እና አዛኝ::1.1 3.አል-መሊክ፦ በግዛቱ ያሻውን የሚፈጽም ንጉስ:: 59.23 4.አል-ቁዱስ፦ ሊታሰብ ከሚችል ባህሪ ሁሉ የጸዳ::59.23 5.አስ-ሰላም፦ ሰላሙን በፍጡራኑ ላይ የሚያሰፍን::59.23 6.አል-ሙእሚን፦ የተናገረውን የሚያጸድቅ ታማኝ::59.23 7.አል-ሙሀይሚን፦ በምሉእ ችሎታው ሁሉንም ነገር የሚቆጣጠር:: 59.23 8.አል-ዓዚዝ፦ አቻ የለሽ ሐያልና አሸናፊ:: 59.23 9.አል-ጀባር፦ ፈቃዱን በሐይል የሚፈጽም፣ ጠጋኝ እና ፈዋሽ::59.23 10.አል-ሙተከቢር፦ የልዕልና ባህሪያቱ ብቸኛ ባለቤት::59.23 11.አል-ኻሊቅ፦ ፍጡራንን በፈቃዱ የፈጠረ::59.23 12.አል-ባሪእ፦ ፍጡራንን በፈቃዱ ያስገኘ::59.23 13.አል-ሙሶዊር:- ለእያንዳንዱ ፍጡር የተለየ ቅርጽ የሰጠ::59.23 14.አል-ገፋር፦ መጥፎ ድረጊትን ይቅር የሚል::20.82 15.አል-ቀህሃር፦ አምባነገኖችን ሁሉ የሚያሸንፍ::12.39 16.አል-ወህሃብ፦ በችሮታው የሚያንበሸብሽ::3.8 17.አል-ረዛቅ፦ ሲሳዮችን የሚሰጥ::51.59 18.አል-ፈትታሕ፦ ለባሮቹ የችሮታውን ካዝናዎች የሚከፍት::32.26 19.አል-ዓሊም:- በእውቀቱ ሁሉንም ነገር ያካበበ::2.158 20.አል-ቃቢድ:- ከፍጡራኑ ለሚሻው፣ የፈለገውን ነገር የሚነሳ::2.245 21.አል-ባሲጥ :- ምስጢራቱን ለሚሻው አካል የሚያካፍል::2.245 22.አል-ኻፊድ:- ካሐድያንና ወንጀለኞችን ዝቅ የሚያደርግ::56.3 23.አር-ራፊዕ:- ወዳጆቹን ከፍ የሚያደርግ::58.11 24.አል-ሙዒዝ:- እርሱን ለሚታዘዙ አማኞች ክብር የሚለግስ::3.26 25.አል-ሙዚል:- ከሀዲያንን የሚያዋርድ::3.26 26.አስ-ሰሚዕ :- ፍጡራንን ሁሉ የሚሰማ:: 2.127 27.አል-በሲር:- ፍጡራንን ሁሉ የሚመለከት::4.58 28.አል-ሐኪም:- የነገሮችና የፍርዶች ሁሉ መመለሻ::22.69 29.አል-ዓድል:- በግዛቱ ውስጥ ነውር ወይም ጉድለት የሌለበት::6.115 30.አል-ለጢፍ:- ለባሮቹ የሚያዝን::6.103 31.አል-ኸቢር:- ግልጽም ስውርም የሆኑ ነገሮችን ሁሉ የሚያውቅ::6.18 32.አል-ሐሊም:- ለቅጣት የማይቸኩል::2.235 33.አል-ዐዚም:- ከአእምሮ ግንዛቤና ችሎታ በላይ የሆነ::2.255 34.አል-ገፉር:- ጠላቱን የሚምርና ተውበትን የሚቀበል::2.173 35.አሽ-ሸኩር :- ባሮቹን የሚመነዳ::35.30 36.አል-ዐሊይ:- ከሁሉ በላይ የኾነው::4.34 37.አል-ከቢር :- ከአልባሌ ነገሮች የጠራ::13.9 38.አል-ሐፊዝ:- ፍጡራንን ከመናጋት የሚጠብቅ::11.57 39.አል-ሙቂት:- ለፍጡራን ቀለባቸውን የሚፈጥር እና የሚያከፋፍል::4.85 40.አል-ሐሲብ:- የፍጡራንን ጉዳይ በፍትህ የሚተሳሰብ::4.86 41.አል-ጀሊል:- ልእልናውና ምሉእነቱ የላቀ::55.27 42.አል-ከሪም :- ስጦታው የማይነጥፍ::27.40 43.አር-ረቂብ:- ፍጡራንን የሚያውቅና የሚከተታተል::4.1 44.አል-ሙጂብ:- ዱዓን ተቀባይ::11.61 45.አል-ዋሲዕ :- እውቀቱ በጊዜና በቦታ የማይወሰን::2.268 46.አል-ሐኪም:- ከምሉእነቱ ጋር የሚቃረኑ ተግባራትን ከመፈጸም የጠራ::31.27 47.አል-ወዱድ:- ፍጡራኑን የሚወድ::11.90 48.አል-መጂድ:- በማንነቱም ሆነ በስራው የላቀ::11.73 49.አል-ባኢሥ:- ሙታንን ለምርመራ የሚቀሰቅስ::22.7 50.አሽ-ሸሂድ :- ግልጽም ስውርም የሆኑ ጉዳዮችን ሁሉ የሚመለከት::4.166 51.አል-ሐቅ:- ከሁሉንም ነገር የላቀ እውነት::6.62 52.አል-ወኪል:- የሁሉንም ጉዳዮች ሐላፊና ከዋኝ።3.173 53.አል-ቀዊይ:- ምንም ነገር የማይሳነው::22.40 54.አል-መቲን:- ምንም ነገር የማያሸንፈው::51.58 55.አል-ወሊይ:- በወዳጆቹ ተወዳጅ፣ የነርሱ ረዳትና አለኝታ::4.45 56.አል-ሐሚድ:- ለምስጋናና ለውዳሴ ተገቢ::14.8 57.አል-ሙሕሲ:- ጥቃቅን ጉዳዮች የማያመልጡትና ታላላቆች የማይሳኑት::72.28 58.አል-ሙብዲእ:- ፍጡራንን መጀመሪያ ካልነበሩበት ያስገኘ ፈጣሪ::10.34 59.አል-ሙዒድ:- ፍጡራንን ወደ ሞት የሚመልስ::10.34 60.አል-ሙሕይ:- የበሰበሱ አጥንቶችን ዳግመኛ ሕያው የሚያደርግ::70.158 61.አል-ሙሚት:- ነፍስን ከአካል በመነጠል የየሚያሞት::7.158 62.አል-ሐይ:- ያለና የሚኖር ሕያው::2.255 63.አል-ቀዩም:- ሁሉንም ነገር ያለ ረዳት የሚያከናውን::2.255 64.አል-ዋጅድ:- የሚፈልገውንና ያሻውን ሁሉ ማግኘት የሚችል::38.44 65.አል-ማጅድ:- የተላቀ ችሮታና በጎ ምግባር ባለቤት::85.15 66.አል-ዋሒድ:- በህላዌው አንድ የሆነ::2.163 67.አል-አሐድ:- በማንነት አንድ የሆነ::112.1 68.አስ-ሰመድ:- ጉዳዮች የሚከጀሉበት መጠጊያ::112.2 69.አል-ቃዲር:- ሁሉንም ነገር ያለ ረዳት የሚያከናውን ሁሉን ቻይ::6.65 70.አል- ሙቅተዲር:- የሻውን ነገር የሚወስን::18.45 71.አል-ሙቀዲም:- ከፍጡራን የሚሻውን የሚያስቀድም::16.61 72.አል-ሙአኽኺር:- ጠላቶቹን ከእዝነቱ በማራቅ የሚያዘገይ::71.14 73.አል-አወል:- ሁሉንም ነገር የቀደመ::57.3 74.አል-አኺር:- ፍጡራን ከጠፋ በኋላ ወደኋላ የሚቀር::57.3 75.አዝ-ዛሂር:- በምልክቶቹ፣ በተአምራቱና በአድራጎቱ ግልጽ የሆነ::57.3 76.አል-ባጢን:- ከእይታ የተሰወረ፣ ሚስጥራትን ሁሉ አዋቂ:: 57.3 77.አል-ዋሊ:- የነገሮች ባለቤት፣ በችሮታው ውለታ የሚውል።13.11 78.አል-ሙተዓል:- ደረጃው ከፍ ያለ፣ በክብሩና በሕልውናው የላቀ::13.9 79.አል-በር:- ለለመኑት ቸር::52.28 80.አት-ተዋብ:- ከባሮቹ ተውበትን ንስሃን የሚቀበል::2.128 81.አል-ሙንተቂም:- ብቀላው የሚፈራ::32.22 82.አል-ዓፍዉ:- ወንጀልን የሚያብስ::4.99 83.አር-ረኡፉ :- ለባሮቹ በጣም አዛኝ::3.30 84.ማሊከል ሙልክ:- በንግስናው የፈለገውን የሚያደርግ::3.26 85.ዙልጀላሊ ወልኢክራም:- የልእልናዎችና የልቅናዎች ሁሉ ባለቤት::55.27 86.አል-ሙቅሲጥ:- ፍትሕ አስፋኝ ፍትሐዊ::7.29 87.አል-ጃሚዕ:- ሁሉ የሰበሰበ ሰብሳቢ::3.9 88.አል-ገንይ:- አንዳች ነገር የማይከጅል ሐብታም::3.97 89.አል-ሙግኒ:- ከባሮቹ ለሚሻው ሰው የሚሰጥ::9.28 90.አል-ማኒዕ:- ባሮቹን ለመጠበቅ የሚያቅብ::67.21 91.አድ-ዷር:- ከባሮቹ የሚሻውን የሚጎዳ::6.17 92.አን-ናፊዕ:- የመጥቀም ባለቤት::30.37 93.አን-ኑር:- የእውነተኞችን ልቦናዎች የሚያበራ::24.35 94.አል-ሃዲ:- ሁሉንም ነገር የፈጠረና የመራ::22.54 .95.አል-በዲዕ:- ጥበበ-ረቂቅ ፈጣሪ::2.117 96.አል-ባቂ:- ዝንተ ዓለም የሚኖር::55.27 97.አል-ዋሪስ:- ፍጡራንን ሁሉ ወራሽ::15.23 98.አር-ረሺድ:- የሚመራ አመላካች::2.256 99.አስ-ሰቡር:- የሚታገስ፣ የማይቸኩል። 2.153