አሰፋ አባተ

ከውክፔዲያ

አሰፋ አባተ ደግሞውም «የማሲንቆው አባት»ተብሎ የሚጠራ ሲሆን ታዋቂ ኢትዮጵያዊ ድምፃዊ ነበር።

የሕይወት ታሪክ[ለማስተካከል | ኮድ አርም]

አሰፋ አባተ በ፲፱፻፳፱ ዓ.ም. በወሎ ክፍለ ሀገር የጁ ሳንቃ ቀበሌ ተወለደ። አሰፋ ፱ ዓመት እንደሞላው በድምፁ ግሩምነት ተደንቆ በደሴ ቤተ መንግሥት ሥራ ጀመረ። ከዚያም በ፲፱፻፵፩ ዓ.ም. ወደ አዲስ አበባ በመምጣት በሀገር ፍቅር ማህበር ተቀጠረ።

የሥራዎች ዝርዝር[ለማስተካከል | ኮድ አርም]

አሰፋ አባተ በሙዚቃው ዓለም ለአጭር ጊዜ እስከቆየበት ጊዜ ድረስ ፶ የሚሆኑ ዜማዎችን ተጫውቷል። ከነዚህ መካከል «ዓሳ አበላሻለሁ ዓባይ ዳር ነው ቤቴ» እና «የማትበላ ወፍ በጭራ ተይዛ» ይጠቀሳሉ።

ማጣቀሻ[ለማስተካከል | ኮድ አርም]