አው ባድር

ከውክፔዲያ

ኣው-ባዲር፣ አው-ባድር፣ አባዲር፦ (ዑመር አርሪዳ) (በግምት ወደ ፲፫ ኛው ክ/ዘ)፦ በ ፲፫ ኛው ክ/ዘመን ውስጥ የተፃፈውና ስለ ሐረር ጥንታዊ አፈታሪካዊ ታሪክ የሚዘክረው 'ፋዝ መዲናት ሐረር' የተባለው ያልታተመ መጽሐፍ እንደሚገልጸው አባድር (ዑመር አርሪዳ) እጅግ ከተከበሩት የሐረር ሼኽዎች ውስጥ አንዱና ዋንኛው ናቸው። በዚሁ መጽሓፍ አገላለጽ መሠረት፡ አባድር ከሌሎች በርካታ ሼኾች ጋር በመኾን ከሂጃዝ በ፮፻፩፪ ሂጅሪያ (1216 እ.ኤ.አ) ተነስተው ሐረር ከገቡ በኋላ በአካባቢው የጎሣ እና ኃይማኖት መሪዎች ተመርጠው ዒማም ሆኑ። በቀጣዮቹ ዓመታትም፡ ከተከታዮቻቸው ጋር በመሆን የዚህ ዘመን ፖርቱጋላዊያን ወይም ጣልያኖች ይሆናሉ ተብለው በሚገመቱት የአአዋሚ ንጉሥ ካርቢናል ብ. ማኅራዋል፣ በልጁ ጁርኒያል፣ በሴት ልጁ ማርቃኒሽ(ስ) እና በወንድሙ ሣያደር ላይ በርካታ ጦርነቶችን መርተዋል። እነዚህ ጦርነቶች የተካሄዱት በሐረር ዙርያ ባሉ አካባቢዎች ነው።

አባድር በሐረር የአሚሮች ሥም ዝርዝር ውስጥም ሥማቸው ተጠቅሷል። ከዚህ አኳያ ሦስት ዘመናት ከአባድር የግዛት ዘመናት ጋር ተዛምደዋል። እነዚሀም ከ፫፻፩-፬፻፭ ሂጅሪያ (1000-1014 እ.አ.አ)፣ ቀጥሎም ከጥቂት የተቋረጡ የግዛት ዘመናት በኋላ ከ ፬፻፭-፬፻፲፩ ሂጅሪያ፣ እንዲሁም ስማቸው እስከ አኹን ካልታወቁ ገዢዎች የሥልጣን ዘመናት በኋላ ከ፬፻፶፰-፶፱ ሂጅሪያ ባሉት ጊዘያት ውስጥ አባድር አካባቢዉን መርተዋል። አህመድ አስ-ሣሚ የተባለ ጸሓፊ ጃድዋል አስ-ሣስ ወስ-ሣሚ በተባለው መጽሓፉ የአባድርን የግዛት ዘመን ከ ፫፻፴፫-፫፻፶፫ ሂጅሪያ ያደርገዋል። ይህ ስሌት አሳማኝነቱ ያጠራጥራል፤ ምክንያቱም በአው-ባድር የዘር ሐረግ መሠረት፡ ከመጀመሪያው ከሊፋ ኣቡበከር አስ-ስዲቅ (ረዲ አላሁ አንሁ) እስከ አው-ባድር ዘመን ድረስ፡ የሓያ አምስት ትውልድ ልዩነት ሲስላ ፊት ከተጠቀስው ቁጥር ጋር ስለማይሄድ ነው። ከተገለጹት ዘመናት ውስጥ የፋዝ ዘገባ ከአሚሮች ሥም ዝርዝርና የግዛት ዘመናት እና ከአስ-ሣድ የአውባድር ዘመን ቆጠራዎች በተሻለ ከአው-ባድር የዘር ሐረግ ቆጠራ ስሌት ጋር ይቀራረባል።

በተለይም በሐረር፡ እስከዚህ ዘመን ድረስ አው-ባድርን የሚያወድሱ፣ የሚዘክሩ በርካታ ዝክሪዎች በየቀኑ ይዘከራሉ። በጥንታዊቷ የሐረር ከተማ ውስጥ፡ የሚገኘውና በአካባቢው ሕዝቦች የሚዘየረው የአው-ባድር የቀብር ሥፍራና ቤት-መስጊድ፡ እንዲሁም ቤት-አሩስ አው-ባድር፦ አው-ባድር የሐረሪ ሤት ያገቡበት ተብሎ የሚታመነው ቤት ሥፍራዎች ለአብነት ይጠቀሳሉ። የአው-ባድር ዝናና መልካም ምግባራት ከሐረር ውጪ ባሉት የኢትዮጵያና አካባቢዋ ባሉ ሙስሊሞች ጭምር በጣም ይከበራሉ፣ ይዘከራሉ።

ከአው-ባድር (ዑመር አር-ሪዳ) ሌላ ተመሳሳይ ስም ያላቸው ዑለማዎች በሐረር አቅራቢያ በተለያዩ ዘመናት ኖረዋል። እነኝህም ታላላቅ ዑለማዎች አባድር ሳይህ ዑስማን፣ አባድር ባያዚድ፣ እና ባዴ አባድር ናቸው።

27 መድሃኒያለምና ሙስሊሟ ሀረር እኛ እርስበእርስ ስንናከስ ወይናደጋማዋ ሐረር እርስ በእርሱ ከሚበላላው ጅብ ጋር ሳይቀር ተግባብቶ የሚኖርባት ከተማ ናት፡፡

  ሐረር ከአዲስ አበባ ደቡብ ምሥራቅ በአምስት መቶ ኪሎሜትር ርቀት ላይ የምትገኝ የምስራቅ ኢትዮጵያ ከተማ ናት። በዘመኑ የአስተዳደር መዋቅር የሃረሪ ክልል ዋና ከተማ ናት። በ1,885 ሜትር ከፍታ ላይ፣ የወይና ደጋ የአይር ጠባይ በተላበሰ ቦታ ላይ አርፋለች።  በ1987 ዓመተ ምህረቱ የህዝብ ቆጠራ መሰረት ሐረር 76,378 ሕዝብ ይኖርባታል።

ሐረር ለዘመናት ከፍተኛ የንግድ ማዕከል ሆና ስትኖር ከመኻል አገር፣ ከአፍሪካ ቀንድ እና ከአረብ አገራት ጋር በንግድ መንገዶች ስትገናኝ ከቀሪው አለም ጋር ደግሞ በቀይ ባሕር ወደቦች አማካኝነት ትገናኝ ነበር። የሐረር ጀጎል ግንብ ከ1998 ጀምሮ በዩኔስኮ የዓለም ቅርስ ዝርዝር ውስጥ ይገኛል። በእስልምና ሃይማኖት "4ኛዋ የተቀደሰች ቦታ" ተብላም ስትታወቅ 82 መስጊዶች፤ አንዳንዶቹ ከ10ኛው ክፍለ ዘመን ጀምሮ የነበሩ፤ እንዲሁም 102 የቀብር ቦታዎች አሉዋት

 ኣው-ባዲር፣ አው-ባድር፣ አባዲር፦ (ዑመር አርሪዳ) (በግምት ወደ ፲፫ ኛው ክ/ዘ)፦ በ ፲፫ ኛው ክ/ዘመን ውስጥ የተፃፈውና ስለ ሐረር ጥንታዊ አፈታሪካዊ ታሪክ የሚዘክረው 'ፋዝ መዲናት ሐረር' የተባለው ያልታተመ መጽሐፍ እንደሚገልጸው አባድር (ዑመር አርሪዳ) እጅግ ከተከበሩት የሐረር ሼኽዎች ውስጥ አንዱና ዋንኛው ናቸው። በዚሁ መጽሓፍ አገላለጽ መሠረት፡ አባድር ከሌሎች በርካታ ሼኾች ጋር በመሆን ከሂጃዝ በ፮፻፩፪ ሂጅሪያ (1216 እ.ኤ.አ) ተነስተው ሐረር ከገቡ በኋላ በአካባቢው የጎሣ እና ኃይማኖት መሪዎች ተመርጠው ዒማም ሆኑ። 
የሀረር ሕዝብ ታሪክ ፣ ባህል እና ማንነት ከሀረር ከተማ ጋር በእጅጉ የተቆራኘ ነው፡፡ ሀረሪዎች በረዥም ዘመን የሥልጣኔ ታሪካቸው ያፈሯቸው ተንቀሳቃሽ እና የማይንቀሳቀሱ እንዲሁም የሚዳሰሱ እና የማይዳሰሱ በርካታ ቁሳዊ እና መንፈሳዊ ቅርሶች ባለቤት ናቸው፡፡ ከእነዚህ ቅርሶች መካከልም የከተማዋ ልዩ መለያ ምልክት ከመሆንም አልፎ እ.ኤ.አ በ2006 በአለም ቅርስነት የተመዘገበው የጀጎል ግንብ በቀዳሚነት ይጠቀሳል፡፡በግንቡ ውስጥም ከ82 በላይ መስኪዶች እና በርከት ያሉ የሀረሪ ባህላዊ ቤቶች ይገኛሉ፡፡

ሀረር ከፍተኛ የስልጣኔ እድገት ደረጃ ላይ በደረሰችበት በ16ኛው ክፍለ ዘመንም በምሥራቅ አፍሪካ የእስልምና ሀይማኖት ትምህርት እና የንግድ ማዕከል ሆናም አገልግላለች፡፡ ይህም የበርካታ ታሪካዊ እና ባህላዊ ቅርሶች ባለቤት እንድትሆን አድርጓታል፡፡ የጀጎል ግንብ የሀረሪ ህዝብ የኪነ ህንፃ ችሎታውን የሚያስመሰክር የታሪክ እና የጥበብ መዘክር ነው፡፡ ይህ ግንብ በ16ኛው ክፍለ ዘመን አጋማሽ በአሚር ኑርአማካኝነት እንደተገነባም ይነገራል፡፡ሐረር እንኳን ዛሬ ቀን ዘምኖ ትናንትናም ቢኾን ስንቱ ባሕር አቋርጦ የከተመባት፤ ስንቱ ቅጥሯ ገብቶ ለትውልድ የተረፈ ትዝታ ያስቀመጠባት የውበትና የጥበብ መዲና ናት፡፡ የኢትዮጵያ ኢስላማዊ ኪነ ህንጻና ባህል ማንምም ሳይመስል፤ ሃይማኖታዊ መሰረቱን ሳይጥል የነገሰባት መዲና፤ ያው ጀጉልን መዞር ነው፡፡ በየቦታው መቆም፡፡ በየቦታው ማየት….በየቦታው መደምም…ጀጉልን ገብተው ይኖሯታል እንጂ አይጽፏትም፡፡

ጀጉልን ውስጥ ለውስጥ ከጀመርናት መቆሚያ የለውምና ከጊዜ እየተሻማን በበራፍ በበራፍ እንለፍ

ሀረር ከቅርስነት ባሻገር እ.ኤ.አ በ2003/4 በሰላም ፣ በመቻቻል ፣ በመፈቃቀር እና በልማት ከተማነት አለም አቀፍ ሽልማት እና እውቅናን አግኝታለች፡፡ ይህም የተለያየ እምነት ፣ ባህል እና ቋንቋ ያላቸው ህዝቦች ለዘመናት በሰላም እና በፍቅር የኖሩባት እና ዛሬም የሚኖሩባት ከተማ በመሆኗ የተቀዳጀችው ክብር እና እውቅና ነው፡፡ ሀረር ዩኔስኮ ዕውቅናን የቸራት በዓለም ቅርስ ብቻ አይደለም፡፡ ከኪነ ህንጻዎቿ ልቀት ባለፈ ህያው ሆኖ ዛሬም እየኖረ ባለው ሰዋዊ እሴት ምርጥ ነሽ ብሏታል፡፡ ፈረስ መጋላ ይሉታል ሀረሮች ከፊት ለፊቱ የአሚር አብዱላሂ አደራሽ አለ፡፡ ሀረር መድኃኒዓለም በር ላይ፡፡ ጀጉል በሀገራችን በርካታ መስጂዶች የሚገኙባት ከተማ ናት፡፡ በግንብ የተከበበው ቅጥሯ ውስጥ የሚገኘው የመድኃኒዓለም ቤተ ክርስቲያን ከተማዋ ዩኔስኮ የተባለውን ዓለም አቀፋዊ ትኩረት ስባ የመቻቻልና የሰላም ተምሳሌት የተባለ እውቅና እንድትቀበል አድርጓታል፡፡ በረዣዥም የመስጂድ ሚናራዎች የታጀበው የሀረር መድኃኒዓለም ቤተ ክርስቲያን በ27 በድምቀት ይነግሳል፡፡ የጀጉል መንገዶች ከጁምአ ዕለት ድምቀት በተጨማሪ በተለየ 27 ነጠላ ለባሾች ከየአሉበት ወደ ቅጥሯ የሚገቡበት ሌላ ትዕይንት ያስተናግዳሉ፡፡ ምዕተ ዓመት የተሻገረው ይህ ቤተ ክርስቲያን ንጉሰ ነገስቱ አጼ ምኒሊክ ኢትዮጵያን በሚመሩበት ራስ መኮንን የሀረርጌ ገዢ በነበሩበት ዘመን የታነጸ ነው፡፡ ያሰሩት ራስ መኮንን ናቸው፡፡ ክቧ ቤተክርስቲያን ውብ ናት፡፡ ዛፎቿ ጥቂት ናቸው ነገር ግን ከግቢዋ ስፋት አኳያ ጥሩ አድርገው አጅበዋታል፡፡ ዛሬ ከኹሉም አቅጣጫ ሰው ወደ ጀጉል እያመራ ነው፡፡ ሐረር ወይም ዱክ በር ከሚባለው በሗላ በተሽከርካሪ ማለፍ አይቻልም፡፡ ይሄ አጋጣሚ ሌላ ትዕይንት ፈጥሯል፡፡ ነጠላ ያጣፉ ጧፍ የያዙናና ሂጃብ የለበሱ መንገደኞች በጋራ እየተሳሳቁ መንገዱን ሞልተውታል፡፡ እጣንና ጧፍ የዘረጉ ነዋየ ቅድሳት የሚሸጡ መንገዱን ዳርና ዳር ይዘውታል፡፡ የኔ ቢጤዎች ስለ መድሐኒያለም እያሉ ይለምናሉ፡፡ መላው የሐረር ሕዝብ አቦ እንወድኻለን! ሀገርን ለማጥፋት ለመበታተን ቀን ከሌት የሚተጋ መንግስት መሳይ ጊዜ አንግሶት እየገዛን ቢኾንም አንተም እንደኛው በቁምም በስጋም እየሞትክ ቢሆንም አብሽሩ እኛ አንድ ኾነን ሽ የኾንን ኢትዮጵያውያን ነን! የመጣብንን ሰይጣናዊ የጥፋት ውሃ ከአምላክ ጋር አንድ ከኾን እናከሽፈዋለን!!! "ኢትዮጵያ" ማለት መንፈስ ነው፣ እሱም "አንድነት" ማለት ነው፡፡ ኢትዮጵያ የፍቅር ሀገር የመቻቻል ምድር ለዘላለም ትንሩልን!!!!

ምንጭ፦[ለማስተካከል | ኮድ አርም]

ኢ. ዋግነር፣ ዘ ዲክሽነሪ ኦፍ ኢትዮጵያን ባዮግራፊ፣ ገጽ 1፣ ቮልዩም 1፣ በአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ የኢትዮጵያ ጥናት ኢንስቲትዩት፣ አዲስ አበባ፣ ኢትዮጵያ።