አዲስ ዘመን (ከተማ)

ከውክፔዲያ
አዲስ ዘመን
አዲስ ዘመን ከተማ
ከፍታ 1975 ሜትር
የሕዝብ ብዛት
   • አጠቃላይ 24,849
አዲስ ዘመን is located in ኢትዮጵያ
{{{alt}}}
አዲስ ዘመን

12°07′ ሰሜን ኬክሮስ እና 37°47′ ምሥራቅ ኬንትሮስ


አዲስ ዘመንደቡብ ጎንደር የሚገኝ ከተማ ሲሆን ከባሕር ዳር ወደ ጎንደር ከተማ በሚጓዘው መንገድ መካከል ይገኛል። በድሮ ስሙ ደብረ አብርሃም ሲባል፣ በአሁኑ ጊዜ የከምከም ወረዳ አስተዳደር ማዕከል በመሆን ያገለግላል።

ከአዲስ ዘመን ከተማ አጠገብ ከሚገኙ ታዋቂ ቦታዎች የደብረ ገላውዲዎስ ገዳም፣ የዋሻ እንድሪያስዋሻ ተክለሃይማኖት አብያተ ክርስቲያናት እና አስባ ተራራዎች ይገኛሉ። ታሪካዊው ጉዛራም እንዲሁ በቅርብ ይገኛል። ደብረ ገላውዲዎስ በዓፄ ገላውዲዎስ ዘመን በነበረ ቅዱስ ሰው የተመሰረተ ሲሆን በቆዩ የግድግዳ ምስሎቹና ከ16ኛው ክፍለ ዘመን በሚመነጩ የወይራ ዛፎቹ ይታወቃል። በኋላ በ1572ዓ.ም. አንድ የኦሮሞ ነገድ በንጉሱ በዓፄ ሱሰንዮስ ላይ ዘመቻ ሲከፍት የዓፄ ሠርፀ ድንግል እናት ወደዚህ ቦት ደብረ አብርሃም መጥታ እንደተጠለለች ታሪክ ይዘግባል[1]

አዲስ ዘመን፣ ከ1956-1972 ዓ.ም የሊቦ አውራጃ ማዕከል በመሆንም አገልግሏል። በ1958 በተደረገ የህዝብ ቆጠራ አዲስ ዘመን ውስጥ 4400 ሰዎች የነበሩ ሲሆን፣ ከደብረ ማርቆስ የሚመጣው የስልክ አገልግሎት እዚህ ከተማ ደርሶ ነበር። በአጠቃላይ 3 ቢሮዎች እና 2 ግለሰቦች የስልክ አገልግሎት ተጠቃሚ ነበሩ።

የሕዝብ ስብጥር[ለማስተካከል | ኮድ አርም]

የአዲስ ዘመን ሕዝብ ቁጥር [2][3]
ዓ.ም.** የሕዝብ ብዛት የተማሪዎች ብዛት
1958
4,400
548
1976
9,100
1986
14,342
1993
17,600
1997
24,849


ማጣቀሻ[ለማስተካከል | ኮድ አርም]

  1. ^ Richard Pankhurst, The Ethiopian Borderlands (Lawrenceville: Red Sea Press, 1997), p. 288
  2. ^ http://www.nai.uu.se/library/resources/dossiers/local_history_of_ethiopia/A/ORTAC05.pdf
  3. ^ CSA 2005 National Statistics, Table B.4