እምቧይ
እምቧይ (Solanum incanum) ኢትዮጵያ ውስጥ የሚገኝ ተክል ነው።
የተክሉ ሳይንሳዊ ጸባይ[ለማስተካከል | ኮድ አርም]
ቊጥቋጣም ዕጽ አንድ ሜትር ይደርሳል።
ይህ ተክል ባጠቃላይ መርዛም ሲሆን፣ በማስለመድ በኩል የባዚንጀን (Solanum melongena) አያት ሆነ።
አስተዳደግ[ለማስተካከል | ኮድ አርም]
በብዛት የሚገኝበት መልክዓ ምድር[ለማስተካከል | ኮድ አርም]
በኢትዮጵያ ግዛት በሰፊው የተስፋፋ ነው። ባጠቃላይ በተፈጀ መስክ ወይም መንገድ ዳር በጣም ተራ ነው።
የተክሉ ጥቅም[ለማስተካከል | ኮድ አርም]
ድቡልቡል ፍሬዎቹ ደማቅ ብርቱካን ሲሆኑ ልጆች ለመቅሰም ይፈተናሉ፤ ስለዚህ በልጆች መመረዝ ይደርስባቸዋል። ጥርሱም በዘለቄታ የተበለዘ፣ የተጎዳ ይሆንባቸዋል።
ከሽንት ጋር በመቃላቀል ፍሬው በቆዳ ፋቂ ፍብሪካ ውስጥ፣ ወይም ጨብጡ ለማከም ተጠቅሟል።[1]
ሥሩም ለአሚባ በሽታ ወይም ለእባብ ነከስ ይኘካል።[2]
ጅምር! ይህ አጭር ጽሑፍ መሠረት ወይም መዋቅር ነው። አሁን ሊያስፋፉት ይችላሉ! |
- ^ አማረ ጌታሁን - SOME COMMON MEDICINAL AND POISONOUS PLANTS USED IN ETHIOPIAN FOLK MEDICINE Archived ጁላይ 31, 2017 at the Wayback Machine March 1976 እ.ኤ.አ.
- ^ የፍቼ፣ ኦሮሚያ ባህላዊ መድሃኒት ጥናት 2006 ዓም ከዓቢዩ እኒየው እና ሌሎች፣ ጎንደርና አዲስ አበባ ኡኒቨርሲቲዎች ሥነ ፍጥረት ኮሌጆች