ኩዋላ ሉምፑር

ከውክፔዲያ

ኩዋላ ሉምፑር (Kuala Lumpur) የማሌዢያ ዋና ከተማ ነው። በክላንግና በጎምባክ ወንዞች የሚጋጠሙበት ሥፍራ ሆኖ የስሙ ትርጉም «ጭቃማ መጋጠሚያ» ነው። የተሠራው በቻይና ሠራተኞች በ1849 ዓ.ም. ነበር።

ኩዋላ ሉምፑር
KL + Putrajaya locator.png

የሚኖርበት የህዝብ ቁጥር የአካባቢውን ኗሪ ሲጨምር 7.2 ሚሊዮን ሰዎች ሆኖ ሲገመት የራሱ የከተማው ኗሪ ቁጥር ደግሞ 1,887,674 ሆኖ ይገመታል። ከተማው 03°08′ ሰሜን ኬክሮስ እና 10°42′ ምሥራቅ ኬንትሮስ ላይ ተቀምጦ ይገኛል።