ኪቶ

ከውክፔዲያ

ኪቶ (Quito፣ በኦፊሴሉ San Francisco de Quito /ሳን ፍራንሲስኮ ዴ ኪቶ/) የኤኳዶር ዋና ከተማ ነው።

የሚኖርበት የህዝብ ቁጥር የአካባቢውን ኗሪ ሲጨመር 2 ሚሊዮን ሆኖ ሲገመት፣ የራሱ የከተማው ኗሪ ቁጥር ደግሞ (1997 ዓ.ም.) 1.5 ሚሊዮን ሆኖ ይገመታል። ከተማው 00°14′ ደቡብ ኬክሮስ እና 78°30′ ምዕራብ ኬንትሮስ ላይ ተቀምጦ ይገኛል።

ከጥንት ጀምሮ ከተማ በዚህ ስፍራ ነበር። የኢንካ መንግሥት ከተማውን በ1500 ዓ.ም. ገዳማ ያዙት። ነገር ግን ስፓንያውያን በደረሱበት ጊዜ በ1525 ዓ.ም፤ እንዳይማረኩት የኢንካ አለቃ ሩሚኛዊ ከተማውን ፈጽሞ አቃጠለው። ከዚያ ስፓንያውያን በ1526 ሳን ፍራንሲስኮ ዴ ኪቶ ብለውት እንደገና ሠፈሩበት። በ1533 ዓ.ም. ሥፍራው በይፋ 'ከተማ' ተብሎ ተሰየመና ከ1555 ዓ.ም. ጀምሮ ለአውራጃው መቀመጫ ሆነ።



San Francisco Plaza, «ኪቶ» Quito

«ኪቶ» Guápulo de Quito[ለማስተካከል | ኮድ አርም]


TelefériQo