ክብደት

ከውክፔዲያ

ክብደት በአንድ ቁስ ላይ የመሬት ስበት የሚያሳርፍበት የጉልበት መጠን ማለት ነው። መሬት ላይ የአንድ ነገር ክብደት ከነገሩ ግዝፈት በንዲህ መልኩ ይለካል፦

W = mg,
  • W ክብደት ነው
  • m የነገሩ ግዝፈት ነው
  • g= 9.8 m/s^2 ሲሆን በመሬት ስበት ምክንያት የሚፈጠረው የቁሶች ፍጥንጥነት ነው;

በርግጥ ቁሶች በመሬት ብቻ ሳይሆን የሚሳቡት በሌሎችም ቁሶች ይሳባሉ። ይህ ክስተት ግስበት ይሰኛል። ለምሳሌ በጨረቃ ወይም ፀሐይ ወይም ማርስ። ባጠቃላይ መልኩ ቁሶች በግስበት ሜዳ ውስጥ ሲገኙ የሚያርፍባቸው የስበት ጉልበት ክብደት ተብሎ ይታወቃል።

የግስበት መጠን ከአንድ ቁስ መካከለኛ ቦታ እየራቅን በሄድን ቁጥር በርቀቱ ስኩየር መጠን ግስበቱ እየደበዘዘ ይሄዳል። በዚህ ምክንያት የግስበቱ ሜዳ ደከመ እንላለን። የመሬትም ስበት ከባህር ወለል ተነስተን ወደ ተራራማው የምድር ክፍል እየወጣን ስንሄድ ግስበቷ እየደበዘዘ ይሄዳል። ስለዚህም የአንድ ቁስ ክብደት በተራራ ላይ ሲቀንስ በባህር ወለል ላይ ይጨምራል። ይህ ጸባይ ከግዝፈት ጋር ይለያያል። የአንድ ነገር ግዝፈት የትም ቦታ አንድ አይነት ነው።