ውክፔዲያ:ታሪካዊ ማስታወሻዎች/መጋቢት 4

ከውክፔዲያ

መጋቢት ፬

  • ፲፱፻፶፯ ዓ/ም - መሬት አልባነትን ለማስወገድ የዩኒቨርሲቲ ኮሌጅ ተማሪዎች በፓርላማው ፊት ለፊት ተሰልፈው «መሬት ለአራሹ የምትሹ፤ ተዋጉለት አትሽሹ» የሚለውን መዝሙራቸውን ለመጀመሪያ ጊዜ አሰሙ።
  • ፲፱፻፷፩ ዓ/ም - በኢትዮጵያ የተመደቡ (ሦስት የሩሲያ ጋዜጠኞችና ሦስት የቼኮዝሎቫኪያ ዲፕሎማቶች)፤ ለተማሪዎች እንቅስቃሴ የገንዘብ እርዳታ አድርገዋል በሚል ወንጀል ከአገር እንዲባረሩ ተደረገ።
  • ፳፻፭ ዓ/ም - የአርጀንቲናው ተወላጅ፣ ካርዲናል ጆርጅ ማርዮ በርጎግልዮ የሮማ ካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን መንበረ ጴጥሮስ ፪መቶ፷፮ኛው ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት (ፓፓ) ኾነው ቀዳማዊ ፖፕ ፍራንሲስ ተብለው ተመረጡ።