ውክፔዲያ:ታሪካዊ ማስታወሻዎች/ሚያዝያ 5

ከውክፔዲያ
  • ፲፭፻፳፬ ዓ/ም - አይፈርስ አምባ በተባለ ስፍራ ከግራኝ መሀመድ ጋር በተደረገ ጦርነት ራስ እስላም ሰገድ፣ ተክለ ኢየሱስ እና ብዙ መኳንንት ሞቱ።
  • ፲፱፻፵፫ ዓ.ም. ፦ ፪ ሺህ ፻፷፰ ወታደር ያሰለፈው የኢትዮጵያ የክቡር ዘበኛ ሠራዊት፣ ቃኘው የሻለቃ ጦር ወደ ኮርያ ዘመተ። ከዘማቾቹ ማህል አንዱ የነበረው ‘የክራሩ ጌታ’ የ፶ ዐለቃ ካሣ ተሰማ "እልም አለ ባቡሩ" በሚለው ዘፈኑ ይሄንን ዕለት አወድሶታል።
  • ፲፱፻፶፮ ዓ/ም - አንጋፋው የፊልም ተዋናይ ሲድኒ ፗቲዬር ‘ሊሊስ ኦፍ ዘ ፊልድ’ (Lilies of the Field) በተባለው ፊልሙ የ’ኦስካር’ ሽልማት ሲቀበል የመጀመሪያው ጥቁር አሜሪካዊ ነው።