ውክፔዲያ:ታሪካዊ ማስታወሻዎች/ታኅሣሥ 27

ከውክፔዲያ

ታኅሣሥ ፳፯

  • ፲፰፻፹፰ ዓ/ም - ዊልሄልም ሮንትገን የተባለ ጀርመናዊ፣ ኤክስሬይ ብሎ የሠየመውን ጨረር እንዳገኘ በአውስትሪያ ጋዜጣ ላይ ተዘገበ።
  • ፲፱፻፸፯ ዓ/ም - የ፳ኤል መንግሥት ‘ኦፐሬሽን ሙሴ’ በሚል ሥያሜ ኢትዮጵያውያን ፈላሻዎችን ከኅዳር ፲፪ ቀን ፲፱፻፸፯ ዓ/ም ጀምሮ በድብቅ ወደ ፳ኤል ካጓጓዘ በኋላ የዚህ ምሥጢራዊ የአየር ውፅዓተ-ነገድ ወሬ በመሰማቱ በዛሬው ዕለት የማቆሚያ ትዕዛዝ ተላለፈ። በዚህ የስድስት ሳምንት ውፅዓት ፰ሺ ፈላሻዎች ሲሰደዱ ከ፮ ዓመት በኋላ በተደገመው ‘ኦፐሬሽን ሰሎሞን’ ደግሞ ፲፭ሺ አይሁዳዊ ኢትዮጵያውያን ወደ ፳ኤል ተሰደዋል።