ውክፔዲያ:ታሪካዊ ማስታወሻዎች/ታኅሣሥ 29
- ፲፰፻፸፱ ዓ/ም የሸዋው ንጉሥ ምኒልክ ሠራዊትና የሐረሩ አሚር ዐብዱላሂ ሠራዊት በሜታ ወረዳ፣ ምሥራቅ ሐረርጌ ውስጥ በምትገኘው ጨለንቆ ላይ ገጥመው ከ፴ ደቂቃ ውጊያ በኋላ የዐሚሩ ሠራዊትተሸንፎ ወደሐረር ሸሸ። ወዲያው ሐረር በሸዋው ንጉሥ እጅ ገባች።
- ፲፱፻፷፭ ዓ/ም የአፍሪቃ አንድነት ድርጅት የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሮች፤ አረባዊ ነዳጅ አምራች አገሮች በወቅቱ የነዳጅ ምርታቸውን የፖለቲካ መሣሪያ በማድረጋቸው በአፍሪቃውያን አገሮች ላይ የሚያስከትለውን ተጽዕኖ ለማጥናት አዲስ አበባላይ ተሰበሰቡ።