የነጩ ቢትወደድ መጽሐፍ

ከውክፔዲያ
(ከየላውድ አቆጣጠሮች የተዛወረ)

የነጩ ቢትወደድ መጽሐፍ (እንግሊዝኛThe Book of the White Earl ወይም Bodleian Laud Misc. MS 610) በ1450 ዓም ገደማ በአይርላንድ የተፈጠረ ሥነ-ጽሑፋዊ፣ ሃይማኖታዊ ወይም አፈታሪካዊ ክምችት ነው። በአይርላንድኛ በ«ነጩ ቢትወደድ» ጄምዝ በትለር፣ የኦርሞንድ 4ኛው እርል (ቢትወደድ) ሲሆን በርሱ ደጋፍ ነበር የተጻፈው። በክምችቱ ውስጥ «የወንጉስ ሰማዕታት ዝርዝር» በ820 ዓም ያህል እንደተቀነባበረ ይታስባል፤ ሌሎች ክፍሎች ከ1160 ዓም እንደ ሆኑ ይመስላል።

በይዞታው መጨረሻ «የላውድ አቆጣጠሮች» የተባለው ሰነድ ይጨመራል፤ ይህ የአይርላንድ ነገሥታት ዝርዝር በሙሉ ከስላንጋ እስከ ማይል ሰቅናይል ማክ ዶምናይል ድረስ ይሰጣል። እነዚህ የአይርላንድ ከፍተኛ ነገስታት እስከ 1014 ዓም ገዙ፤ ሰነዱም በዚያው ወቅት ያህል አሁን ከጠፋው «የካሼል መዛሙርት» ዝርዝር ተቀድቶ እንደ ተዘጋጀ ይታመናል። ስለዚህ በሌቦር ጋባላ ኤረን ከተገኘው ዝርዝር (1065 ዓም ግድም) ይልቅ ጥንታዊ ነው።

ውጭ መያያዣ[ለማስተካከል | ኮድ አርም]