የምዕራብ ንጉሥ እናት

ከውክፔዲያ
«የምዕራብ ንጉሥ እናት» የሸክላ ቅርስ፣ 200 ዓ.ም ግድም ተሠራ

«የምዕራብ ንጉሥ እናት» (ቻይንኛ፦ «ሺ ዋንግሙ») በቻይና አፈ ታሪክ ትገኛለች።

ቀርከሃ ዜና መዋዕል ዘንድ፣ በንጉሥ ሹን ፱ኛው ዓመት (2052 ዓክልበ. ግድም) መልዕክተኞች ከምዕራብ ንጉሥ እናት (ሺ ዋንግሙ) ወደ ሹን ግቢ መጥተው «የነጭ ድንጋይ ቀለበቶችና የዕንቁ የቀስተኛ ጣት ቤዛዎች» ስጦታ አቀረቡ። በሌላ ምንጭ (ሹንዝዕ) የሹን ተከታይ ዳ ዩ የሺ ዋንግሙ ተማሪ ነበረ።

ከዚህ በኋላ በቻይና አረመኔ ሃይማኖት ሺ ዋንግሙ እንደ ሕያው ሴት አምላክ ተቆጠረች። በሥነ ቅርስ ከሻንግ ሥርወ መንግሥት (1700 ዓክልበ. ግድም) የተቀረጸ አጥንት በጸሎት ይጠቅሳታል። በ950 ዓክልበ. አካባቢ የነገሠው ዦው ሙ እንዳገኛት በትውፊት ይባላል። በ4ኛው ክፍለ ዘመን ዓክልበ. ላውዝዕ ያስተማረው የዳው ሃይማኖት ደግሞ እስካሁን እንደ ሴት አምላክ ያያታል። በተጨማሪ የቻይና ነገሥታት ጪን ሽኋንግ (250 ዓክልበ. ግድም) እና ሃን ዉ (100 ዓክልበ. ግድም) እንዳገኙአት በትውፊት ይባላል።