የአውስትራሊያ ንጉሣዊ በራሪ ሐኪም አገልግሎት

ከውክፔዲያ
የRFDS አውሮፕላን ማቆሚያ

የአውስትራሊያ ንጉሣዊ በራሪ ሐኪም አገልግሎት (Royal Flying Doctor Service ወይም ባጭሩ Flying Doctor በራሪ ሐኪም) ከ1928 እ.ኤ.አ. ጀምሮ በአውስትራሊያ ሰፊ ምድረ በዳ በአውሮፕላን የሚዘዋወር የሕክምና አገልግሎት ነው።

መጀመርያ በ1928 እ.ኤ.አ. «የአውስትራሊያ ምድረገብ ሚስዮን አየራዊ ህክምና አገልግሎት» (Australian Inland Mission Aerial Medical Service) ተብሎ በፕሮቴስታንት ሰባኪና የአውትራሊያ ምድረገብ ሚስዮን መስራች ክቡር ጆን ፍሊን ተመሠረተ። በ1934 እ.ኤ.አ. ስሙም «የአውስትራሊያ አየራዊ ሕክምና አገልግሎት» (Australian Aerial Medical Service) ሆነ። በ1942 እ.ኤ.አ. ደግሞ ስሙ እንደገና ተቀይሮ «በራሪ ሐኪም አገልግሎት» (Flying Doctor Service) ተባለ። በ1955 እ.ኤ.አ. በንግሥት እልሳቤት ጥብቅና ድጋፍ በይፋ «ንጉሣዊ» (Royal) ተጨምሮ ተሾመ።

ብዙ ሆስፒታሎች ሊቆሙበት ባልተቻላቸው በአውስትራሊያ ምድረ በዳ ለሚገኙት በሽተኞች፣ በራሪ ሐኪሞች በአየር ይደርሳሉ። መድኃኒትና ህክምና ከማቅረባቸው በላይ በሽተኛውን ደግሞ ወደ ሜዳ ሆስፒታል ሊያደርሱ ይችላሉ።

ብዙ የቴሌቪዥን ትርዒቶች የበራሪ ሀኪሞችን ኑሮ አብራረዋል፣ ከነሱም The Flying Doctor (1959-60 እ.እ.አ.)፤ The Flying Doctors (1986-93 እ.እ.አ.)፤ R.F.D.S. (1993-94 እ.እ.አ.)፤ RFDS: Royal Flying Doctor Service (2021 እ.እ.አ.-አሁን) ፣ እንዲሁም ፊልሙ The Flying Doctor በ1936 እ.እ.አ. ተሠራ።