የኻዛር መንግሥት

ከውክፔዲያ
የኻዛር መንግሥት 650-850 ዓም ግድም

የኻዛር መንግሥት (የኻዛራውያን ኻጋነት ወይም ኻዛርያ) በከፊል ዘላን የሆነ የቱርኪክ ሕዝብ ግዛት ሲሆን፣ የቀድሞው ኦኖቅ ኻጋናት መንግሥት በቻይናውያን ሥራዊት በ650 ዓም በተሰበረበት ጊዜ፣ ከቅሬቶቹ ከተነሡት በስሜን ካውካሶስ አውራጃ ዋናው ተተኪ ኃይል ሆነ። ኻዛርያ ይህን አውራጅ እስከ 951 ዓም የኪየቫን ሩስ መንግሥት እስካሸነፋቸው ድረስ ይገዛ ነበር።

732 ዓም ግድም የኻዛርያ መንግሥት ወደ ተልሙድ አይሁድና ገብቶ የአገሩ መንግሥት ሃይማኖት እንደ ሆነ ይመስላል። ከዚያው በፊት የቱርኮች ጥንታዊ አጓጉል እምነት (የተንግሪ ሃይማኖት) ነበሩ።