የወርቃማ ጎል

ከውክፔዲያ

የወርቃማ ጎል በእግር ኳስ፣ ዘመናዊ ገና (Field hockey) እና የበረዶ ላይ ገና (ice hockey) ባሉ ጨዋታዎች በመደበኛው ሰዓት እኩል የወጡ ሁለት ቡድኖች በተጨማሪ ሰዓት ቀድሞ ጎል ያስቆጠረ የሚያሸንፍበት ህግ ነው። ይህ ህግ ወጥቶ የነበረው እ.አ.አ. በ1992 የነበረ ሲሆን በዓለም አቀፉ የእግር ኳስ ማህበር (FIFA) በኩል እ.አ.አ. በ2004 ውድቅ ሆኗል። ከወርቃማ ጎል በተጨማሪ ብራማ ጎል የሚባልም ህግ አለ።