የዶሮ ጉንፋን

ከውክፔዲያ

የዶሮ ጉንፋን ወይም ኤቭያን ፍሉ (Avian Flu) ኢትዮጵያን እንደ ማንኛውም ኣገር ያሰጋታል። ይህ የወፍ ኢንፍሉኤንዛ ወይም የዶሮ ጉንፋን እያጠቃ ያለው ኣንዳንድ የሩቅ ምሥራቅ እስያ ኣገሮችን ቢሆንም ወደ ኤውሮፓኣፍሪቃ መስፋፋት ጀምሯል። እስካሁን (፳፻ ዓ.ም.) በሽታው የገደላቸው ሰዎች ብዛት ከ300 ያነሱ ሲሆን በሽታውን ለመቆጣጠር ከ150 ሚሊዮን ዶሮዎች በላይ ተፈጅተዋል።

ያለውም ዋና ስጋት ቫይረሱ ከታመመ ዶሮ ሰው ጭምር ስለሚይዝና እራሱንም መቀያየር ስለሚችል ቀስ በቀስ ጉንፋኑ ከሰው ወደ ሰው የመተላለፍ ችሎታ ኣፍርቶ ሕዝብ እንዳይፈጅ ነው። ከዚህ በፊት ኢንፍሎኤንዛ በመደጋገም በዓለም ላይ ብዙ ሚሊዮን ሕዝቦች ገድሏል። ስለዚህ ስለበሽታው ሕዝቡ በሚገባ ማወቅና መዘጋጀት ኣለበት። በሽታው ኣንድ ቦታ ያሉትን ዶሮዎች በ48 ሰዓታት ሊፈጅ ይችላል። ኣንዳንድ ኣእዋፍ ወደተለያዩ ኣገሮች ስለሚበሩ በሽታውን መከላከል ቀላል ባይሆንም የመከላከያ ክትባት ኣለ። ለሰው መድኃኒትና መከላከያ የመሥራትም ጥድፊያ ቀጥሏል። በብዛት የሞቱ ኣእዋፍ ሲታዩ ለባለሥልጥኖች መንገር እንጂ ኣለመነካካትና ድመቶች እንዳይበሏቸው መከላከል ያስፈልጋል። በሽታው ካለበት ኣገር ዶሮን ኣለማስገባትና የጓሮ ዶሮን ኩስ ማጸዳዳት ጠቃሚ ናቸው። ዶሮንና እንቁላልን ለመብላት በሚገባ ማብሰል ቫይረሱን ይገድለዋል።

የውጭ መያያዣዎች[ለማስተካከል | ኮድ አርም]