ደብረ-ዕንቁ ወይብላ ማርያም

ደብረ-ዕንቁ ወይብላ ማርያም በደቡብ ጎንደር ዞን ፡ በደብረ ታቦር ከተማ የምትገኝ ጥንታዊት ቤተ ክርስቲያን ናት።ደብረ ዕንቁ ወይብላ ማርያም በ 1610 ዓመተ ምኅረት በአጼ ሱስንዮስ ዘመነ መንግስት በእትየ ማርታ አማካኝነት እንደተመሠረተች ታሪክ ይናገራል፡፡ከስሟም አንጻር ወይበይኝ ብለው ይጠሯታል፡፡በፊተኛው ዘመን ጳጳሳት ከነገስታት ጋር አብረው ይኖሩ ነበርና የአጼ ሱስንዮስ ቤተመንግስት የነበረው አሪንጎ አቦ ዝቅ ብሎ ስለነበረ አማራ ሳይንት ቀሲስ መንክርና ቀሲስ አስፋው የሚባሉ ካኅናት በጳጳሳቱ ፅላት ለማስባረክ ይዘው መጥተው አስባርከው በሚመለሱበት ጊዜ በአሁኑ የቅዱስ ሩፋኤል ፅበል ቦታ ሲደርሱ ታቦተ ሕጉ ወይም ፅላቱ አልሔድም ትላቸዋለች፡፡በዚህም ለሶስት ቀናት ድንኳን ደኩነው ካደሩ በኋላ በሶስተኛው ቀን አንዲት ንጉሱን ደጅ ለመጥናት ከትግሬ የመጣች እንስት ስሟ ማርታ የተባለች ሰው ካኅናቱ ለ 3 ቀን ምግብ ሳይመገቡ ድንኳን ተክለው አገኘቻቸው፡፡ ማርታም ምን እያደረጋችሁ ነው ብላ በጠየቀቻቸው ጊዜ ታቦት አስባርከን ወደቦታዋ ወደ አማራ ሳይንት ይዘን ልንሔድ ብንል ማንሳት ተሳነን ይሏታል፡፡እርሷም የሴትነት ግዳጅ አለብኝ ነገር ግን እናቴ ናትና ወይ በይኝ ብላት አትፀናብኝም በማለት በጉልበቷ በርከክ ብላ ብትጠይቃት ወይ በይኝ ብላት ወይ ትለኛለች በማለት ስፀልይ ያች ታቦቷ ተነሳችላት፡፡ ያኔ ቦታው የአፄ ሱስንዮስ የፈረስ ማደሪያ ነበርና ቦታውን አስጠርጋ ታቦቱን አምጥታ አስገብታ ወደ ንጉሱ በምትሔድ ሰዓት ታሪክ አጥፊዎች ፈረሶቹን አባርራ ታቦት አስገባሁ አለች ብለው ተናግረው ነበርና ንጉሱ ሴትዮዋን ሲያይ ደስተኛ አለበረም፡፡ ንጉሱም ካኅናቱ ገብተው ቅዳሴ ገብተው ከሆነ ታቦቲቱ እንዳትወጣ ካልተቀደሰ ደግሞ ታቦቲቱ ትውጣ ብለው ሲያዝዙ ሲትዮይቱም ማርታ ሆዴን እያምመኝ አስቸግሮኛል አሞኛል እያለች ከፈረስ እየተሰቀለች እየወረደች ብምትጓዝ ጊዜ ካኅኑ አስፋው ስረይ ካኅን ሆኖ በሚቀድስ ጊዜ አሁን በጌ ምድር ተብሎ በሚጠራው ስፍራ የአሁኑ ኮሌጅ ላይ እግዚኦ ሲባል ሰማች ማርታም ይሔው ተቀድሷል አለች፡፡ በዚህም ፅላቲቱ ባለችበት ቦታ እንድትኖር ተፈቀደ ቦታውም ከበረ፡፡
| ጅምር! ይህ አጭር ጽሑፍ መሠረት ወይም መዋቅር ነው። አሁን ሊያስፋፉት ይችላሉ! |
[[መደብ:የኢትዮጵያ አብያተ ክርስቲያናት]