ቁስቋም ማርያም

ከውክፔዲያ

ደብረ ፀሐይ ቍስቋም ማርያምጎንደር ከተማ በስተ ስሜን ምዕራብ ወጣ ብሎ በሚገኘው በደብረ ፀሐይ ቁስቋም የተሰራ ቤተክርስቲያን ነው። ደብረ ፀሓይ ቁስቋም በእቴጌ ምንትዋብ፣ ከ1725 ዓ.ም. እስከ በ1738ዓ.ም. ተገንብቶ የተጠናቀቀ ሲሆን በጊዜው 360 መስታዎቶች የነበሩት፣ በቀይና ሰማያዊ ሃር አልባሳት ያሸበረቀ፣ እንደ ደብረ ብርሃን ስላሴ በጥሩ ኪነት የተዘጋጀ፣ ከወርቅና ከብር የተሰሩ የቤተ ክርስቲያን ማገልገያወች የነበሩት፣ በጊዜው የተደነቀ ቤተ ክርስቲያን ነበር። ደብረ ፀሐይ በተመሰረተበት ዘመን የራሱ ጉልት የነበረው ሲሆን ይኼውም በእብናትበለሳ እና አርማጭሆ ተሰባጥሮ ይገኝ ነበር፤ ስለሆነም 260 ቀሳውስትን በስሩ ያስተዳድር ነበር፡፡ ከህንጻ ይዘቱ አንጻር በዚሁ ዘመን በምንትዋብ ከተገነባው ናርጋ ስላሴ ጋር ይመሳስል እንደንበር ግንዛቤ አለ።

የቁስቋም ግቢ ሦስት ጊዜ ጉዳት ደርሶበታል። በመጀመሪያ በ1858፣ ዓፄ ቴዎድሮስ መቅደላ ሊያሰሩት ላሰቡት ቤተ ክርስቲያን ከቤተክርስቲያኑ የተለያዩ ንዋያትን መውሰዳቸው ነበር። ሁለተኛው ጉዳት የደረሰው በ1870ወች፣ ደርቡሾች ግቢውን በእሳት በማጋየት ያደረሱት ዋናው ጉዳት ነበር። በዚህ ቃጠሎ ቁስቋም ማርያም ሊፈርስ ችሏል። ቤተክርስቲያኑ አሁን የያዘውን ቅርጽ ያገኘው በጣሊያኖች ጊዜ ሲሆን ያሁኑ መልኩ ከድሮው እጅግ ይለያል። የእቴጌ ምንትዋብ፣ የልጇ ዳግማዊ እያሱ እና ልጅ ልጇ እዮዋስ አጥንቶች በመስታዎት ሳጥን ሆነው በዚህ ቤተክርስቲያን ይገኛሉ። ከእሳት የተረፉ የእቴጌ ምንትዋብ መገልገያዎች አሁን ድረስ በቤተክርስቲያኑ ይገኛሉ።

ቁስቋም ማርያም በደርቡሾች ተቃጥሎ እንደነበር - 1930 ዓ.ም. [1]

-1px

ማጣቀሻ[ለማስተካከል | ኮድ አርም]

  1. ^ Monti, Augsto,I castelli di Gondar , Societa Italiana Arti Grafiche Editrice, Rome 1938